መነሻ ገጽ The BiG Interview “ከጅማ አባጅፋር የለቀኩት ገንዘብ ተቀብዬ ወይም ሙስና ሰርቼ አይደለም ይሄ ስም ማጥፋት ነው” “ድሮ ቀለበት ያደረገ ተጨዋች ሽማግሌ ነበር የሚባለው” አሰልጣኝ ክፍሌ ቦልተና (ሰበታ ከተማ)�
The BiG Interview

“ከጅማ አባጅፋር የለቀኩት ገንዘብ ተቀብዬ ወይም ሙስና ሰርቼ አይደለም ይሄ ስም ማጥፋት ነው” “ድሮ ቀለበት ያደረገ ተጨዋች ሽማግሌ ነበር የሚባለው” አሰልጣኝ ክፍሌ ቦልተና (ሰበታ ከተማ)�

አጋራ
አጋራ

THE BIG INTERVIEW WITH : KIFLE BOLTENA

 

በዮሴፍ ከፈለኝ

ሀትሪክ፡- ሰበታ ከተማን እንዴት
ተቀላቀልክ.. ውድድርስ ነበረው?

ክፍሌ፡-ሰበታን ለማሰልጠን በጣም እፈልግ
ነበር… ቤቴ እዚያው አካባቢ ነው ለመስራትም
ይመች ስለነበር ባገኝ አልጠላም ነበር፡፡ ነገር
ግን ክለቡን ለማሰልጠን ጥያቄ አላቀረብኩም
ስራ አስኪያጁ ታዬ ናኔቻ የ3 አሰልጣኞችን
ስም በዕጩነት አቀረበ.. ማቅረቡንም ደውሎ
ነገረኝ ለግምገማ አሉ የሚባሉ ደጋፊዎች
ተጠርተው ስፖርት ቢሮው ተሰበሰቡና በሙሉ
በአንድ ድምፅ መረጡኝ የሜዳ፣ የደጋፊና
የበጀት ችግር የለም የሚል ቅሬታ ነበረባቸው
የክለቡ አመራሮች ጠርተው አነጋገሩኝ ስለኔ
ጀርባ ተነግሮቸው ስለነበር መረጡኝ ይሄ
አመት ካልተሳካ በጀቱ ይቀነሳል ቡድኑ
በጨዋታው ህዝቡን አላስደሰተም ወይም
ውጤት የለም ብለው ተስፋ በቆረጡበት ጊዜ
ነው የገባውት፡፡ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ቡድኑን
ማስገባት ትችላለህ ብለው ሲጠይቁኝ አዎ
መቶ በመቶ ቡድኑን ወደ ሊጉ አሳድገዋለሁ
ብዬ ቃል ገብቼ ስራውን ጀመርኩ፡፡ በእርግጥ
ውጤት ቢጠይፋ ግማሽ አመት ላይ የስራ
ባልደረቦቼ እንደተሰናበቱ ሁሉ እንደምሰናበት
አውቅ ነበር፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ቃልህ
በምንም መንገድ ከታጠፈ ለመባረር ቅርብ
ነው አምላክ ረድቶኝ ኃላፊነቴን በውጤት
በማጀቤ ተደስቻለሁ፡፡

ሀትሪክ፡- ክፍያ ላይ ሰበታ ከተማ ደከም
ብሏል የሚሉ ወገኖች አሉ… አልተቸገርክም?
ክፍሌ፡- በክፍያ ኤሌክትሪክ፣ ወልዲያ፣
አዲስ አበባ ከተማ፣ ኢትዮጵያ መድን ሀዲያ
ሆሳዕና ይበልጡናል
ወደ 7ኛ ደረጃ ላይ ነው
የምንገኘው… ባለፉት
አመታት ግን በክፍያ
ሰበታ ከላይ ነበር፡፡ አሁን
ስፈርም ትልቁ 44 ሺ
ብር የሚከፈላቸው 5
ተጨዋች ብቻ ናቸው፤
የሌሎቹን ቀንሰህ
አስፈርም ተብዬ ነው
ያስፈረምኩት፡፡ ብዙ
ተጨዋቾች በተሻለ
ክፍያ ቡድኑን ለቀው
ወጥተዋል፡፡ ለዝግጅት
አዳማ ስሄድ 12
ወጣቶችን ይዤ ነው…
አዳማ የነበረን የሙከራ
ጊዜ እንጂ የዝግጅት
ጊዜ አይመስልም ነበር
ሰበታ በነዚህ ልጆች
እንዴት ፕሪሚየር ሊግ
ለመግባት ያስባል?
ክፍሌ ከ3 ጨዋታ
በላይ አይዘልም
ይባረራል ይሉኝ ነበር፡
፡ ዝግጅት በደንብ
ሳንሰራ ወደ ሰበታ
ተመለስን የመጀመሪያ
የወዳጅነት ጨዋታ
ስናደርግ በአዳማ 5ለ0
ተሸነፍንና ብዙ ሰው
ሳቀብን፤ እኔ ግን 32
ተጨዋቾችን አይቼ
ተጠቀምኩበት ከዚያ
በኋላ በየጨዋታው
እያስተካከልን ተስፋ
ሰጪ እንቅስቃሴ
እያየሁ መጣሁ…
ከመጀመሪያው ጨዋታ
ጀምሮ ጥሩ ሆንን
ከቡና ቢ የተገኙ፣
በሌሎች ክለቦች
የተሰላፊነት እድል
ያጡ… ሌሎች ልምድ
ያላቸው ተጨዋቾችን
አካተን የፈጣሪ ፍቃድ
ታክሎበት ውጤታማ
ሆንን፡፡ ሊጉን ስንጀምር
ኮምቦልቻን 2ለ1
ረታን ከዚያ በኋላ
ው ጤ ታ ማ ነ ታ ች ን
ቀጠለ ተጨዋቾቼ የኔን
የአጨዋወት ፍልስፍና
ተቀብለው ጥሩ አቋም
አሳዩ… ማንኛውም
አሰልጣኝ የራሱ
ፍልስፍና አለው እኔም
ለፍልስፍናዬ በሰጠውት
ልምምድ ደስተኛ ነበሩ ራሣቸውን ለማሳየት
ሲታገሉ ቡድኑን ውጤታማ በማድረጋቸው
ሰበታ ሊያልፍ ችሏል፡፡ ፔፕ ጋርዲዮላ
የእንግሊዝን ኳስ አይቻልም ሲባል ቆየና
በሁለተኛና ሶስተኛ አመቱ በተከታታይ የሊጉን
ዋንጫ አነሳ፡፡ ኳስ ጊዜ ይወስዳል ሰበታ ላይ
ግን በ3 ወር አብሮነት ውጤታማ መሆን
ችለናል፡፡ በከፍተኛ ሊግ ቆይታችን ከባድ ጊዜ
አሳልፈናል የኛን ምድብ ስመለከት ጠንካራ
ፍልሚያ እንደሚጠብቀን ተረድቼ ከቡድኑ
አባላት ጋር ያደረኩት ጥረት ተሳክቶልንና
ዳገቱን ተወጥተን ለድል በቅተናል አንድ
መንፈስ አንድ ልብ ኖሮን ግጥሚያዎቹ
በድል ተወጥተን ሣንሸነፍ ወደ ፕሪሚየር
ሊጉ አድገናል፡፡ በኛ ሀገር ማናጀር አትሆንም
ሙሉ ኃላፊነት ለአሰልጣኝ አይሰጥም
ከኮሚቴ ውስጥ አንዱ ካኮረፈህ አበቃ… ይሄ
ክስተት ሳይኖር በትዕግስት በጋራ ሰርተን
ውጤታማ በመሆናችን ከንቲባ ጽ/ቤት፣
የክለቡ አመራሮች፣ ረዳቶቼና ተጨዋቾቼን
በአጠቃላይ ሁሉንም የቡድኑን አባላት
እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እፈልጋለው፡፡

ሀትሪክ፡- የዳኝነቱ ነገር ጫና ነበረው
ማለት ይቻላል?

ክፍሌ፡- የዳኝነት ችግር ነበር… በውጤት
ደረጃ ካየነው ያለፍነው ለፍተን በላባችን
ነው ይሄን አረጋግጥልሀለሁ፡፡ ከኛ በፊት
እገሌ የሚባል ክለብ 15 ሪጎሬ ነው ያገኘው
ይባል ነበር፤ ገና ድልድል ሲወጣ ፌዴሬሽኑ
የአዲስ አበባ ክለቦች ስለወረዱ ለአዲስ አበባ
ድጋፍ እናደርግ ብሏል ተብሎ ተነግሮን ነበር
ግን በተግባር አላየንም… አንደኛ ዙር ላይ
የነበረብን ጫና ከፍተኛ መሆኑ ግን እውነት
ነው፡፡ ከአንድ ክለብ ጋር ስንጫወት 2
ተጨዋች በቀይ ወጥቶብናል በ8 ተጨዋቾች
1ለ1 ተለያየን፤

ሀትሪክ፡- ቆይ ቆይ…አንተ የተቀጣህበት
ጊዜ ነበር… የውሳኔውን ተገቢነት አትቀበልም?
ክፍሌ፡- በርግጥ ሜዳ ገብቻለው ነገር ግን
የተፃፈው ሪፖርት ልክ አይደለም ያሳፍራል
ዳኛ ከቦ ሊደበድብ ሲል በፖሊስ ታጅቦ ወጣ
ተብሎ 3 ወር ተቀጣሁ… የክለቡ አመራሮችና
ተጨዋቾቼ ደጋፊው ግን ውሸት ስለነበር ከጎኔ
ቆሙ፡፡ ይግባኘ ጠየኩ አዎ ወይም አይ ሳይባል
1500 ብር ከፍዬም ምላሽ ሳላገኝ ቅጣቱን
ጨረስኩ፡፡ ይሄ ያሳፍራል… ክለቡ ይግባኙ
ሳይመለስ ቅጣቱን ስለጨረሰ ያስያዘው ገንዘብ
ይመለስ ብሎ ጠይቆ ያም አልተመለሰም…
እንዲህ አይነት ክፍተት ነበር ከዚያ ውጪ
ወልዲያ ላይ ስንጫወት የኛ በረኛ በ20 ደቂቃ
ውስጥ በቀይ ወጣ ግን በ10 ልጅ አሸንፈን
ተመለስን… ጫናውን ተቋቁመን ያገኘነው
ድል በመሆኑ ነው ድላችንን ልዩ የሚያደርገው
ለፌዴሬሽኑ ለኛ የሚያዳላ ዳኛም አንፈልግም
ግን ፍትሀዊ ውሳኔ የሚሰጥ ዳኛ ይመደብልን
ብለን ጠይቀናል ምላሸ ግን አላገኘንም…
በእርግጥ ለህሊናቸው የሚያጫውቱ ዳኞች
እንዳሉ አንክድም የመጨረሻው ጨዋታ
ከቡራዩ ጋር ስንጫወት ጥሩ ዳኛ ገጥሞናል
የፕሪሚየር ሊግ ዳኛ ተመድቦ 1ለ0 ረታን…
ደሴ ከተማ እኛ ሜዳ ላይ መጥቶ ጥሩ
ዳኛ በማግኘታችን ጠንካራውን ጨዋታ
1ለ0 አሸነፍን… ለገጣፎ ላይ ስንጫወት ጥሩ
ዳኛ በመመደቡ ሁለታችንም ክለቦች ደስተኞች
ነበርን… ጨዋታው ከፍተኛ ትኩረት
ተሰጥቶት ልዩ ኃይል ከሰው እኩል ተመድቦ
በተካሄደ ጨዋታ 1ለ1 ወጥተን በለገጣፎ
ሜዳ ላይ ማለፋችንን አረጋገጥን… ጨዋታው
ከፍተኛ ትኩረት እንደተሰጠው የሚያሳየው
የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ
ጭምር ተገኝተው ተከተትለውታል፡፡
ሀትሪክ፡- በሰበታ ከተማ የአሰልጣኝነት
ቅጥር የተፈፀመው በታዋቂ ደጋፊዎች
ተመርጠህ ነው መሆኑን ገልፀሃል.. አሰልጣኝ
በደጋፊ መመረጡ ተገቢ ነው?

ክፍሌ፡- እንደዚህ አይነት ነገር
አይመረጥም… ነገር ግን ብዙ አሰልጣኝ ባለፉት
8 አመታት ተቀጥረው ሰርተው ውጤታማ
ሳይሆኑ ተሰናብተዋል.. ሰበታን ያልያዘ
አሰልጣኝ ቢቆጠር ትንሽ ነው.. አመራሮቹ
ሰልቸት ብሏቸዋል፡፡ ይህን ለማስወገድ ስራ
አስኪያጁ 3 ሰው በዕጩነት አቅርቧል…
ደጋፊውንም መረጃ ለመጠየቅ ተገደዋል፡
፡ አምናም 30 አሰልጣኝ ለቦታው ተወዳድሮ
በስዩም ከበደ በ1 ነጥብ ተበልጠሀል ተብዬ ነው
የቀረሁት፡፡ በግሌ ለቅጥር ውድድርም መኖሩን
አልደግፍም በየክለቡ የሰከነ ባለሙያ ቢኖር
ለክለቤ ውጤትና ለምንፈልገው አጨዋወት
ይሄ አሰልጣኝ ይሻላል ብሎ መርጦ ቢቀጥር
ነው የሚሻለው፤ አሁን ይሄ የለም፡፡ አሰልጣኙ
እድል ተሰጥቶት ለውጥ ከታየ ለአመታት
በቦታው ላይ እንዲቀመጥ የሚያደርግ ክለብና
አመራር በሀገር ደረጃ እንኳን የለም፡፡

ሀትሪክ፡- ከፕሪሚየር ሊጉ የዋንጫ
አሸናፊነት በላይ ከከፍተኛ ሊግ ወደ ፕሪሚየር
ሊግ ማደግ ከባድ ነው የሚሉ አሉ…
ትስማማለህ?

ክፍሌ፡- እውነት ነው… ዳኛ ለመዳኘት
የሚቸገርበት ሊግ ነው፡፡ ገና ከሜዳ ውጪ
ስትሄድ አቻ ትመርጣለህ.. ዘግተህ 1ለ1
ወይ 0ለ0 ከሆንክ ትደሰታለህ… የአየር ላይ
ኳስ ይበዛዋል ከጨዋታ ውጭ ብትሆንም
ትለቀቃለህ…ሪጎሬ ሊሰጥብህ ይችላል አብዛኛው
ሜዳ አስቸጋሪ ነው የሚዲያ ትኩረትም
የለውም ፌዴሬሽኑ በካሜራ አያስቀረፅም
ይሄ ሁሉ መስተካከል አለበት ከዚህ ውጪ
በታዛቢዎች አላምንም ብዙ ታዛቢዎች ጥሩ
ቢሆኑም ለዳኛ በውሸት የሚያዳሉ ኮሚሽነሮች
አሉ አብረው ስለሚጓዙና የሙያ ባልደረባው
ስለሆነ አጥፍቶም ቢሆን እሱን ማስቀጣት
አይፈለጉም ፖለቲካው ያመጣው ችግርም
አለ… ስለዚህ ህዝብ ይፍረድ ሊጉ የቀጥታ
ስርጭት ይኑረው ሱፐር ሊጉ ላይ አንድም
ካሜራ የለም ካለም ባለሜዳው የሚያቀርበው
ነው ወደ ሊጉ ያለፉት ክለቦች በመርፌ ቀዳዳ
እንዳለፉ ቁጠረው፡፡

ሀትሪክ፡- ሰበታ ከተማ ለዳኞች ምንም
ገንዘብ አልከፈለም እያልክ ነው?

ክፍሌ፡- በፍፁም አላደረግንም… ብንከፍል
ኖሮ እኔ 3 ወር አልቀጣም ነበር፤ ብዙ ነገሮችን
ማድረግ ቀላል ይሆን ነበር… ነገር ግን በዚህ
ውስጥ ሰበታ ከተማ የለበትም ኮምቦልቻ ላይ
4ለ0 ስናሸንፍ ወልዲያን በሜዳው ስንረታ
ደጋፊዎቻቸው እያጨበጨቡ ነው ሆቴል
ድረስ የሸኙን ይሄ መሞገስ አለበት… እኛ በ22
ጨዋታ 1 ሪጎሬ ነው ያገኘነው ይሄ ክለባችን
ውጤትን ያገኘው በራሱ ላብ መሆኑን ያሳያል፡

ሀትሪክ፡- በዳኝነቱ ተበደልን የምትልበት
ጨዋታ የትኛው ነው?

ክፍሌ፡- በሜዳችን ፌዴራል ፖሊስን
ስናስተናግድ የመሀል ዳኛው ሶስት የፍፁም
ቅጣት ምት ከለከለን… ከተጨዋቾቼ ጋር
ተገቢ ባልሆነ ሁኔታ ይመላለሳል.. እልህ
ያስገባቸው ነበር ገና 3ኛ ጨዋታ እንደመሆኑ
ገና ከአሁኑ ለማን አድቫንቴጅ ለመስጠት
ነው? ብለን ጠይቀን ነበር በውሳኔውብንገረምም ሳንሸናነፍ 0ለ0 ተለያየን… ይሄን
መቼም አልረሳውም፡፡ ሁለተኛው ከገላን
ጋር ስንጨወት ሁለት ተጨዋቾች በቀይ
የወጡበትን ጊዜ አልረሳውም… አንደኛው
ጎል አስቆጥሮ ደስታውን ሲገልፅ ማሊያውን
አላወለቀም ነገር ግን ዳኛው ማሊያውን ወደ
ላይ አነሳ ብሎ ቢጫ ካርድ ሰጠው አምስት
ደቂቃ ሳይሞላ ፋውል ሰራህ ብሎ በ5 ደቂቃ
ውስጥ 2 ቢጫ አይቶ የወጣበትን አልረሳውም
በ8 ልጅ መከራችንን አየን… ሁለቱን ዳኞች
መቼም አንረሳቸውም፡፡

ሀትሪክ፡- በፕሪሚየር ሊግና በከፍተኛ
ሊግ መሀል የስም ለውጥ ነው ያለው እንጂ
የደረጃ ልዩነት የለም የሚሉ አሉ… እውነት
ነው?

ክፍሌ፡- በሊጉ ጠንካራ ተፋላሚ የሚሆኑና
ለውጤት የሚፋለሙ የተወሰኑ ክለቦች ናቸው
ሌሎቹ ላለመውረድና ከቻሉ መሀል ሰፋሪ
ለመሆን እንጂ ለውጤት አቅደው የሚመጡ
አይደሉም… በተለያየ ምክንያት ከሜዳ
ውጪ ማሸነፍ ይከብዳል የተጨዋቾች የደረጃ
ልዩነት የለም ምናልባት የአዕምሮ ዝግጅት
ወይም ጫና የመሸከም አቅም ቢለያይ እንጂ
ተመሳሳይ ናቸው፡፡ ጅማ አባጅፋር ወደ ሊጉ
ባደገበት አመት ዋንጫ ወስዷል… ይሄ አንዱ
ማሣያ ነው ከባዱ ነገር የወረዱ ቡድኖች
ወደ ላይ ማደግ መቸገራቸው ነው ኤልፓ፣
ወልዲያ… አርባ ምንጭ…መድን ለማለፍ
ተቸግረዋል…. በእኔም እምነት በሁለቱ ሊጎች
ብዙም ለውጥ የለም፡፡

ሀትሪክ፡- አሰልጣኝ ክፍሌ ቦልተና
የከፍተኛ ሊግ ወይስ የፕሪሚየር ሊግ
አሰልጣኝ?

ክፍሌ፡- ራሴን የማየው የከፍተኛ ሊግ
አሰልጣኝ አድርጌ ነው የማየው… ብዙ
ኔትወርክ የለኝም ደጋፊ የለኝም ይሄ ደግሞ
ከፕሪሚየር ሊጉ አርቆኛል፡፡

ሀትሪክ፡-ኧረ እንዲያውም ኔትወርክ
እንዳለህ ነው የምሰማው?

ክፍሌ፡- (ሳቅ በሳቅ) የለኝም፤.. ውሸት
ነው ቢኖረኝማ ታችኛው ሊግ አልቀርም ነበር..
እንዲሳካልኝ ፈልገው የሚያግዙኝ ሰዎች አሉ
ወጣት ይዘህ ጥሩ ስለምትጫወት ደጋፊህ
ነን የሚሉኝ አሉ.. በማናቸውም ግን ተደግፌ
ክለብ ገብቼ አላውቅም በኔትወርክ የገባሁበት
ክለ የለም አለው ካሉ ይምጡ!

ሀትሪክ፡-የአንተ ስኬታማ ጊዜ መቼ ነው?
ክፍሌ፡- ስኬታማ ጊዜ የምለው በአየር
ኃይል የነበረኝ ጊዜ ነው ዋንጫ አላገኘሁም
ነገር ግን ርካታውን እፈለግ ነበር 25 ሰው
ለአሰልጣኝነት ተወዳደረ የክለቡ አመራር
የነበረው ኮ/ል ገ/ስላሴ የኔን ስም ሲያይ
ውድደሩ ሰረዘና አንተን ነው የምፈልገውና
አለኝ፡ በግሉ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊ በመሆኑ
ስቴዲየም አይጠፋም… አትቅር ብትቀር
ወታደር ይዤ ነው የምመጣው ብሎ ቀልዶ
ቀጠሮ ሰጥቶኝ ሄድኩ… መግቢያ አዘጋጅቶ
ጠብቆ አስገባኝና ቁጭ ብለን አወራን ተግባባን
ሙሉ ኃላፊነቱ ተሰጠኝ… ጥሩ ቡድን ሰራሁ
የደብረዘይት አብዛኛው ነዋሪ የቢሾፍቱ ከነማ
ደጋፊ ነበር.. በኛ አጨዋወት ተማርከና የኛ
ደጋፊ ሆነ… 15 ኦራል መኪና ሙሉ ደጋፊ
መጥቶ ያየን ጊዜ ሁሉ ነበር… ቡድኑን
በነፃነት በምፈልገው መንገድ ሰርቼ ስላሣየሁ
በጣም ረክቻለው ይሄን ጊዜ ልረሳውም፡፡

ሀትሪክ፡- ለአሠልጣኝ ሀጎስ ደስታ ትልቅ
ፍቅር አለህ አሉኝ… እውነት ነው?

ክፍሌ፡- ጋሽ ሀጎስ ነፍሳቸውን ይማርና
ምርጥ አሰልጣኝና መካሪዬ ነበሩ… ቢሮ
ውስጥ ምንም ስለማትሰራ ስልጠና ውሰድ
የምትሰጠው ሀሳብ ጥሩ ነው በትምህርት
አዳብረው ብለው መከሩኝ የፕሮጀክት ስልጠና
ወስድኩ ወዲያውኑ የኤልፓን ሲ ቡድን
ሰጡኝ… አዲስ ተሰጥኦ ያለውን ተጨዋች
ማየት ጀመርኩ ኤልፓ ውስጥ ተጨዋቾችን
መዝገበህ ነው የምትመርጠው …እኔ ግን
ከዚያ ሃሳብ ወጣው.. እነ ዳንኤል የሻውን
ከአፈርሳ ሜዳ ነው ያገኘኋቸው… ብዙዎችን
ከተለያየ ቦታ ወስጄ ፈተንኳቸው በምርጫ ጊዜ
ወደ 3 ሺህ ታዳጊ ይመጣል.. እድሉ ደረጄ
ሲ ሞክሮ ወድቋል ፒያሳ ሲጫወት አይቼ
ግን አመጣሁት… አለማየሁ ዴልፒየሮ 5ኛ
ፖሊስ ጣቢያ አካባቢ አስፓልት ላይ ሲጫወት
ነው ያየሁት፡፡ በሁለት እግሩ የሚጫወት
ተጨዋች ነበር… መልምዬ አጣርቼ ለአገር
የሚጠቅም አንድ ትውልድ አፍርቻለሁ..
ለብሔራዊ ቡድኑም መጥቀም ችለዋል፡
፡ ሰበታም በተመሳሳይ ነው የመለመልኩት..
ተሰጥኦ ያለውን መለየት ርካታ ያለው ጨዋታ
ማየት ያስደስተኛል… በአጠቃላይ በመብራት
ኃይል የነበረኝን ቆይታና የጋሽ ሀጎስ ውለታን
አልረሳውም፡፡

ሀትሪክ፡- በኢትዮጵያ ቡና ቆይታህ ትልቁ
ችግር ምን ነበር?

ክፍሌ፡- ኢትዮጵያ ቡና ውስጥ ከባዱ
ነገር እቅድ አለመኖሩ ነው፡፡ ሪያል ማድሪድ
ባርሴሎናን በገንዘብ ይበልጣል፡፡ ባርሳ
ይህን ለመብለጥ ምን ሰራ የሚለው ነው
ጥያቄው? በአንድ ዘመን የጨዋታ ፍልስፍና
ነው ጋርዲዮላ ከ10 በላይ ዋንጫ ያነሳው…
በወጣት አምኖ ሁለት ሶስት አመት እቅድ
ይዞ መስራት አልያም ገንዘብ አውጥቶ ብሎ
ኮከቦችን መግዛት… ኢትዮጵያ ቡናዎች
ከሁለቱ አንዱን መምረጥ አለባቸው…
በአንዱ ሃሣብ ለማመን የማመንታት
ችግር ነው ያለው፡፡ የደጋፊ መጮህ
የተለመደ ነው ውጤት ከጠፋ ይጮሃል
እቅድ ከያዝክ ተቃውሞን መቻል
አያቅትም… ኢትዮጵያ ቡናን 5
አመት ነው ያሰለጠንኩት…. ሆላንድ
ኮርስ እንድወስድ አድርጎኛል
ለማንም ያላደረገውን ነው ለእኔ
ያደረገው… ውጤት ሲጠፋ ግን
ተሰናበትኩ… እቅድህን ወስነህ
መጓዝ ይጠበቃል.. ይሄ ነው
ችግሩ…. ካሳዬ አሁን ሊመጣ
ነው ይባላል… ቢበላሽበትም
በትዕግስት ጊዜ ሰጥተው መጠበቅ
አለባቸው… ማንቸስተር ሲቲ
ባይታገሰው ጋርዲዮላ 2
ተከታታይ አመት የፕሪሚየር
ሊጉን ዋንጫ አያገኝም ነበር ይሄ
ትዕግስት ይጠበቅባቸዋል ባይ
ነኝ… አንዳንዴ እድለኛ ከተኮነ
ውጤት በአጭር ጊዜ ውስጥ
ሊመጣ ይችላል፡፡ እግዚአብሔር
ረድቶኝ ነው በአጭር ጊዜ የተሳካልኝ፡፡
በእግር ኳስ ግን ትዕግስትና ጊዜ ወሳኝ
መሆኑን ክለቦቻችን ማመን አለባቸው፡፡

ሀትሪክ፡-በኤልፓ ተሰላፊነትህ ምርጡ
ጊዜህ መቼ ነበር?

ክፍሌ፡-ኤሊያስ ጁሃር፣ ጠንክር አስናቀ፣
ክፍሉ መብራቱ፣ እነ ሸዋንግዛው.. እነ አንጀሎ
በነበሩበት ቡድን ውስጥ ቋሚ ተሰላፊ ነበርኩ…
የኢትዮጵያ ሻምፒዮናና የአሸናፊዎች አሸናፊ
ዋንጫን በ1985 ወሰደናል… ሁለትዮሽ
ዋንጫ የወሰደው ይሄ ቡድን ለእኔ ምርጡ
ነበር… በነገራችን ላይ የኤልፓ ባህል ደስ
ይላል… አስቀድሞ ታዳጊውን ቡድን የያዘው
ቢረጋ ነበር ከዚያ እኔ ያስኩ…ቀጥሎ ኤልያስ
ጁሃር አሰልጥኗል… ክለቡን በሚያውቁ
የቀድሞ ተጨዋቾች መሰልጠኑ ነው ምርጥ
ተጨዋቾች እንዲፈሩ ያደረገው… የአሁኑ
የክለቡ ችግር ይሄን ባህል ባለማስቀጠሉ
የመጣ ይመስለኛል፡፡ ሌላው ጥሩ ጎን ያኔ
በእኔ የሰለጠኑት አሁን አሰልጣኝ መሆናቸው
ነው፤ ዳንኤል የሻው፣ ሲሳይ.. ኃይሉ/ቻይና/
እነርሱ ለዚህ ምሳሌ ይሆናሉ፡፡

ሀትሪክ፡- አሁን ግን በታዳጊ ደረጃ
ለመወዳደር የሚፈልግም ወጣትኮ ጠፋ?

ክፍሌ፡- (ሳቅ) አንዴ እድሉ ደረጄ ሲናገር
ሰምቻለው… ከክፍሌ ጋር ለቢ ምርጫ ስንሄድ
ወደ 2 ሺህ ታዳጊ ይመዘገብ ነበር ሁሉም
ስለሚችሉ መምረጥ ይከብደናል… አሁን ግን
ታች ሄጄ ሳይ የመጡት 100 አይሞሉም
አንዱም ግን አይችልም አለ… ችግሩ ታዲያ
የሜዳ ችግር ይሁን ትውልዱ ወይም ተስፋ
መቁረጥ በዝቶ አሊያም ታች ያለው ስልጠና
አልገባኝም …ያኔኮ ትውልዱ ወደ ኳስ
ያዘነብላል ሜዳ እንደጉድ ነበር አሁን ግን ያ
ሜዳ የለም ይሄ ትልቅ ችግር ነው… ሌላው
ደግሞ ተጨዋቹ እስከ 13 አመቱ ድረስ በራሱ
ሊጫወት ይገባል፡፡ ከዚያ በኋላ ቢሰለጥን
ይሻላል ባይ ነኝ አለበለዚያ በአሰልጣኙ ፍላጎት
ይቀረፅና ያለውን ተሰጥኦ ያጣል ይሄ ነው
የሚመስለኝ… ለማን.ዩናይትዶቹ የፈርጊ
ቤቢስ ስኬት የቢ አሰልጣኙን ነው የማደንቀው
ጊግስና ቤካም አብረው ነው ያደጉት የተለያየ
ተሰጥኦ አላቸው ይሄን ጠብቆ ባላቸው ችሎታ
ማሰራቱ ነው ያሳደጋቸው… ጊግስን ድሪብል
ከምታደርግ እንደ ቤካም ረጅም ኳስ ተጫወት
ቢለው አይሆንም… ነገር ግን የሁለቱን
ችሎታ ቡድን ውስጥ መጠቀም ይችላል
ፈርጉሰን ያደረጉት ይሄንን ነው የቢ አሰልጣኙ
ያላቸውን አስቀጠለ እንጂ አላስተዋቸውም
በጣም የማደንቀውም ለዚህ ነው የታዳጊን
አቅም ለማየት የራሱ መነፅር ያለው አሰልጣኝ
ሊኖረን ይገባል፡፡

ሀትሪክ፡- ይህንን የሚያደርግ አሰልጣኝ
አለን ታዲያ?

ክፍሌ፡- (ሳቅ በሳቅ)
ሀትሪክ፡-በኛ ሀገር ደረጃ የራሱ ፍልስፍና
ያለው አሰልጣኝ አለን?

ክፍሌ፡- ስለማንም ማውራት አልሻም
(ሳቅ) ተው… ኳሱ የሚጥመው አንተም
የራስህን እኔም የራሴን
ከተጫወትኩ ነው ሳይንሱ
አንድ ነው አጨዋወቱ
ነው ልዩነት የሚፈጥረው አለበለዚያ ማንም ማሰልጠን
ይችላልኮ ብትወድቅ ብትነሣ በራስ አስተሳሰብ ነው መጓዝ ያለብህ.. ይሄ ካልሆነ ከባድ
ነው፡፡

ሀትሪክ፡-ጨዋታ አይቶ
በማንበብ ምርጥ የምትለው
አሰልጣኝ ማነው?

ክፍሌ፡- የ ኤ ል ፓ ው
ቢረጋ… ስዩም አባተ
ይመቹኛል፡፡ አሁን ደግሞ
በተወሰነ መልኩ ጥሩ ቡድን
እየሰራ ነው የሚባልልት
ምናልባት የማየት እድል ባላገኝም ውበቱ
አባተ ይመስለኛል… ስዩም አባተ ግን ልዩ
ነው ምክትል አሰልጣኝ ሆኜ ሰርቻለሁ
ይደፍራል.. ጎበዝ ነው… ከሁሉም በላይ ግን
ጋሽ ሀጎስ ደስታ ልዩ ናቸው… ታዳጊዎች
ሲጫወቱ ይመለከትና ሁሉንም ዝግጅት
ይዤ ነው የምሄደው ይላል… ዋናውን ቡድን
ተስፋውንና ታዳጊውን ቡድን ሁሉንም
ያያል አሁን ይሄን የሚያደርግ አሰልጣኝ
አለ? የለም.. ዝግጅት ላይ ጠንካራ ከሆኑ በቃ
ተሰላፊ ናቸው ለዚህ ነው ኤልፓ ቤት ከክለቡ
አልፈው ለሀገር የሚጠቅሙ ተጨዋቾች
የሚወጡት… ሌላው አሰልጣኞች ሰከን
ብለው አይሰሩም… ውጤት ተኮር ከሆንክ
ለህይወትህ ነው የምትሰራው ለህይወትህ
ከሰራህ ደግሞ ትክክለኛውን ስራ አትሰራም…
ላለመባረር ለእንጀራ ቤተሰቤ ምን ይበላል
ካልክ ደፍረህ ለመወሰን ትቸገራለህ፡፡ ብዙ
ክለብ የቆ 7 ወይም 8 ተጨዋቾች በአንድ
ክለብ ውስጥ ታያለህ ይሄ ውጤት ላይ
መተኮሩን ያሳያል አሰልጣኙ ታዲያ
ምን እየሰራ ነው እነዚህ ተጨዋቾችኮ
አሰልጣኞች ናቸው አካል ብቃትን
ማስተባበር ነው የአሠልጣኙ ስራ..?
አስተባባሪና አሰልጣኝኮ ይለያያል /
ሳቅ በሳቅ/ መልፋት ታዳጊ ላይ
ማመን ውድቀትም ቢሆን ለህሊህ
ደስታ ይፈጥራል፡፡ ውጪ ሀገር
የሚሰራበት ስልጠና አለ በተለይ
ለኛ ሀገር የሚጠቅመንን ማየት
የኛ ፋንታ ነው እኔም ኤልፓ
እንደነበርኩት አይደለሁም
አሁን.. ያኔ ለእርካታ ነበር
የምጫወተው አሁን ግን ማራኪ
አጨዋወት ከማሸነፍ ጋር የግድ
መሆኑ ገብቶኛል አሰልጣኞች
ወጣት ላይ ማመንና መድፈር
አለብን፡፡

ሀትሪክ፡- ውጤታማ ከነበርክበት
ከጅማ አባጅፋር አሰልጣኝነትህ ለምን
ወጣህ?

ክፍሌ፡- ስሜታዊ መሆኔ ነው…
ስራዬን ለማስከበር የሄድኩበት መንገድ
ልክ አልነበረም ለተጨዋቾች እረፍት
መስጠቴ ነው ያጋጨን… አላባ ላይ 1ኛ
መሆናችንን ስናረጋግጥ ለተጨዋቾቼ እረፍት
ሰጠው 1ኛ ዙር ካለቀ ማረፍ አለባቸው
ብዬ አምናለሁ፡፡ አላባ ላይ እረፍት ስሰጥ
ፕሬዚዳንቱ ሁሴን ደወለና አስተዳደሩ
ይጠብቅሃል ለምን እንዲህ አደረክ አለኝ
ከዚያ በፊትም ለተጨዋቾቼ ፍቃድ ሰጥቼ
ስለነበር ለምን ሰጠህ ብለው መተዳደሪያ
ደንብ አወጡልኝ ከፌዴሬሽኑ ደንብ ውጪ
አልቀበልም አልኳቸው፡፡ 1ኛ ዙር ካለቀ
በኋላ ደካማና ጠንካራ ጎናችንን ለመገምገም
ተቀመጥን… ግምገማው ላይ እያለ እንዲህ
አደረክ ብለው የማይሆን ነገር ሲዘረዝሩ
ተበሳጨሁ… ብድግ አልኩና በዚህ አይነት
ከዚህ በኋላ ብሰራ ውጤታማ አልሆንም
አልኳቸውና ለቀክኩ… በርግጥ በዚህ ተግባሬ
ተፀፅቻለው ይሄ ነው ምክንያቱ በቃ…

ሀትሪክ፡- እኔ የሰማሁት ከ3 ታዳጊዎች
ብር በመቀበልህ መሰናበትህን ነው….ውሸት
ነው?

ክፍሌ፡- በፍፁም… የተሳሳተ መረጃ
ነው… በወቅቱ የነበሩ ሰዎችኮ
አሁንም አሉ እነርሱን መጠየቅ
ይችላል… ከጅማ አባጅፋር
የለቀቅኩት ገንዘብ ተቀብዬ ወይም ሙስና
ሰርቼ አይደለም ይሄ ስም ማጥፋት
ነው፤ ወደፊት እውነቱ ይወጣል
አሰልጣኞች ጋር
ያለ ክፍተት ነው እርስ በርስ
ስ ለማ ን ከ ባ በ ር  ያ ወ ሩ ብ ኝ
አ ሰ ል ጣ ኞ ች አለ… ደስ የሚለኝ
የትም ክለብ ስሄድ ይችላል ነው
የ ም ባ ለ ው … የፊት ለፊት ሳይሆን ማስረጃ
የማይቀርብበት የ ማ ይ ታ ይ ነገር ያወራሉ ይሄ በሽታ
ይ መ ስ ለ ኛ ል ፡ ፡ አንዱ ዋና አሰልጣኝ
ሌላው ምክትል ለመሆን
ሰበታ ድረስ ሄደው አስወርተውብኛል ግን
አልተሳካም… ወደፊት እውነቱ ይወጣል፡፡

ሀትሪክ፡- መጠጥ
ታበዛለህ አሉኝ.. .እውነት
ነው?

ክፍሌ፡- (ሳቅ በሳቅ) ተጨዋች ሣለው
እኔና ኤሊያስ ጁሃር አብረን አንድ ክፍል
ነበር የምናድረው… ሁለታችንም ልንጠጣ
እንጠፋለን እኔና በለጠ ወዳጆ አብረን ነበር
የምናድረው ለሊት ትራስ ሰርተን ሄደን
አሰልጣኝ ወንድማገኝ ከባደ አውቆብናል…
ጠዋት ላይ በሩን ከፍተው ሲያዩ እኛ የለንም
ትራሱን ሲያዩ ስቀው ይወጡና ቁርስ ላይ
ተገናኘን… ደህና መስለን ስንገባ አሰልጣኙ
ወንድማገኝ የተቀበለኝ በጥፊ ነበር (ሣቅ)
አሁን ድረስ ያነሳዋል በዚህ አጋጣሚ ታሟል
ጤናው እንዲመለስ እመኛለሁ፡፡ ረጅም ጊዜ
አልተጫወትኩም ምክንያቱም መዝናናት አበዛ
ስለነበር ነው.. ቤተሰብንና ራስን ለመምራት
ጠጪ ከመሆን መታቀብ አለብን.. ከኔ ልትማሩ
ይገባል ማለት እፈልጋለው. ለነገሩ የአሁኑ
ጊዜ አብዛኞቹ ተጨዋቾች ትዳር ይዘዋል ይሄ
ጥሩ ነው፡፡ መቀጠል አለበት ሰበታ ከተማ
ውስጥ ቀለበት ያሰሩ 2 ተጨዋቾች አሉ በነርሱ
ደስተኛ ነኝ ድሮ ቀለበት ያደረገ ተጨዋች
ሽማግሌ ነበር የሚባለው ድሮኮ ሁለት ሶስት
የሴት ጓደኛ የነበራቸው ተጨዋቾች ነበሩ…
ይሄ አሁን የለም ለአላማ የሚኖር በዝቷል
በዚህ ቀጥሉ ለቀሪ የጨዋታ ህይወታችሁና
ለተስተካከለ ኑሮ መዝናናት ባያበዙ ጥሩ ነው
እላለው፡፡

ሀትሪክ፡- ከሰሞኑ የባለስልጣናትና የጦር
ሰዎች ግድያ መላው ህዝቡ አዝኗል.. ምን
ተሰማህ…?

ክፍሌ፡-ሰው ሲሞት የማያዝን የለም
ወንድም ወንድሙን ሲገድል ተረጋጋቶ
መስራት ይከብዳል የተለየ ሀገር የለንም
አንድ ኢትዮጵያ የሁላችንም ናት፡
፡ በተፈጠረው ድርጊት ቅር ብሎኛል፡
፡ ትክክለኛ ምርጫ ተካሄዶ አሸናፊዎቹ
የሚመሯት ኢትዮጵያ ብትኖር ደስ
ይለኛል፤… ምናልባት በመነጋገር ማመን
አለብን ባይ ነኝ፡፡ ወደ ኋለኛው ዘመን
እየተመለስንኮ ነው አዕምሯችን አድጎ
ማየት እፈለጋለው ወንድም ወንድሙን
ገድሎ ምንም አያመጣም.. ወደ ድህነት
ኋላቀርነት እየሄድንኮ ነው ይሄ መታረም
አለበት ለሟቾች ቤተሰቦች፣ ጓደኞች፣
የቅርብ ሰዎችና ለመላው ህዝቡ መፅናናትን
እመኛለው፡፡

ሀትሪክ፡-የእግር ኳሱ ችግርስ አያሰጋም..
ይሄ ዘረኝነቱ ስጋት አይፈጥርም?
ክፍሌ፡- በጣም ስጋት አለው.. ህዝቡ
የሚወደው እግር ኳስም ሊጠፋ ነው…
የብሔር ስም ያላቸው ቡድኖች መቆም
አለባቸው የከተማ ስም ችግር የለም አለም
ላይም አለ.. ለምን ግን ወደ ብሔር ይሄዳል..?
ፊፋም ይሄን ይቃወማል..? አንዱ ሌላው ጋር
እየሄደ መደብደቡ ፊፋ ጋር አይደርስም ማለት
ይችላል? አንድ ቀን ልንታገድ እንደምንችል
እሰጋለው.. ፌዴሬሽኑ እገዳ ማድረግ ካለበት
መድፈር አለበት… የፊፋና የካፍ ህጎችን
መተግበር የግድ ነው… አለበለዚያ ቀጣዩ ጊዜ
ያሰጋናል፡፡

ሀትሪክ፡-ፎርማቱ ባለበት ይቀጥል ወይስ
ይቀየር?

ክፍሌ፡- ባለበት ይቀጥል ባይ ነኝ…
የችግሩ ምንጭ ፎርማቱ ነው ብዬ አላምንም
ከዚህ ይልቅ ህጎችን ማጥበቅ ነው የሚሻለው…
የፎርማቱ ለውጥ መፍትሄ ያመጣል ብዬ
አላስብም ስፖንሰር ፈልጎ ሁሉም ጨዋታ
በቀጥታ ቢሰራጭ ህዝቡ አይቶ ቢፈርድ
ለውጥ ይኖራል ብዬ አስባለሁ… እግር
ኳስኮ ከዘርና ከፖለቲካ የፀዳ ነው ባያበላሹት
እመርጣለሁ፡፡ ሌላው የፖለቲካ ሰዎች ብቻ
ቢሮ አካባቢ ባይበዙ… አይሁኑ ማለት
አይቻልም መንግሥት ብር ሰጥቶ አይቆጣጠሩ
ማለት አልችልም ነገር ግን የሙያ ሰዎች
በደንብ ቢካተቱ የኳሱ ችግር ሊቀንስ ይችላል
ብዬ አስባለው፡፡

ሀትሪክ፡-ጨረስኩ.. የምታመሰግነው ሰው
ካለ?

ክፍሌ፡- የምስጋና ቅድሚያውን
ለአምላኬ እሰጣለው ፈጣሪዬን አመሰግናለሁ
እግዚአብሔር ይመስገን ብዙ ፈተናዎችን
አልፌ ለዚህ እንደደርስ አድርጎኛል.. ከርሱ
በመቀጠል ውዷ ባለቤቴን ትዕግስት…………..
አመሰግናለው፡፡ ኳስ መጫወት ካቆምኩም
በኋላ የነበረብኝን ደካማ ጎን ችላ ታግሳ
እያበረታታችኝ በትዕግስቷ በምክሯ ደግፋ
ለውጣኛለች፡፡ ስራ አቁሜ ከርሷ የተነሣ ምንም
አይነት ክፍተት አልተፈጠረም እግዚአብሔር
የሰጠኝ እርሷን ነው ረጅም እድሜ
እመኝላታለው ልጆቼን አሳድጌ በህይወት
ኖሬ የተገኘሁት ከእግዚአብሔር ቀጥሎ በርሷ
ነው አመሰግናታለው፡፡ ትዳር ከመሰረትን 20
አመታት ሞልቶናል ቀሪ ዘመናችንን የደስታና
የስኬት እንዲሆን እመኛለው ከዚያ በተረፈ
አዲሱ ከንቲባ፣ ቢሮ ውስጥ ያሉት የክለቡ
ኃላፊዎች፣ ጀግኖቹ ተጨዋቾቼ፣ ረዳቶቼ፣
ጫና ፈጥረው ለድል ያበቁን ደጋፊዎቻችን፣
ቤተሰቦቼን ስኬት እንዲገጥመኝ የተመኙልኝን
ሁሉ ከልብ አመሰግናለሁ፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
The BiG Interviewአዲስአበባ ከተማዜናዎች

“ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ አብዛኞቹ አሰልጣኞች ይልቅ 100 ፐርሰንት ጨዋ ነኝ ብዬ አምናለሁ”

"ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ አብዛኞቹ አሰልጣኞች ይልቅ 100 ፐርሰንት ጨዋ ነኝ ብዬ አምናለሁ"...

The BiG Interviewቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎች

“ዲሲፕሊን ሳታከብርና አንደበትህን ሳትቆጣጠር ለሰው ተምሳሌት መሆን አይቻልም” ስዩም ተሰፋዬ /ኢት.ቡና/

በከፍተኛ ሊግ የእግርኳስ ህይወቱን ጀምሯል...በተጨዋችነት ዘመኑ በታችኛው ሊግ የተጫወተው ለሁለት ክለቦች ለደብረብርሃን...