*… የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ግን ፕሬዝዳንቱ ከውጪ ይምጡና አቋማችንን እናሳውቃለን ብሏል….
በኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ላይ ክስ የመሰረቱት እነ ሻለቃ ሃይሌ ገ/ስላሴ የተፈጠረውን አለመግባባት በዕርቅ ለመጨረስ ከፍርድቤት የቀረበላቸውን ጥያቄ መቀበላቸው ተሰማ።
ትላንት ጉዳኑን የያዘው ችሎት ፊት የቀረቡት ሁለቱ ወገኖች ፍርደ ቤቱ የተፈጠረውን አለመግባባት በዕርቅ እንዲፈቱ ጥያቄ ያቀረበላቸው ሲሆን ከሳሾችና ጠበቆቻቸው በዕርቅ ለመስማማት ፍቃደኛ መሆናቸውን ለችሎቱ ገልጸዋል።
- ማሰታውቂያ -
የተከሳሹ የኢትየጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ጠበቆች በበኩላቸው ዕርቁን እንደሚደግፉት ነገር ግን የኦሎምፒክ ኮሚቴው ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሸብር
ወ/ጊዮርጊስ ሀገር ውስጥ ስለሌሉ ወደ ሀገር ሲመለሱ ከተወያዩበት በኋላ ውሳኔያቸውን እንደሚያሳውቁ የመደበኛ ፍርድቤቱ የህጋዊ ክርክሩ ሂደት ግን እንዲቀጥል ለችሎቱ መጠየቃቸው ታውቋል።
የኢትዮጵያ ቴኒስና ቦክስ ፌዴሬሽኖች ከሻለቃ ሃይሌ
ገ/ስላሴና አትሌት ገዛኧኝ አበራ ጋር በመሆን በኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ላይ ባቀረቡት ክስ ተላልፎ የነበረው የአመራሮች የጉዞ ዕግድና የኦሎምፒክ ኮሚቴው የአካውንት ዕገዳ ተነስቶ የኦሎምፒክ ኮሚቴው የዕለት ተዕለት ስራ መቀጠሉንም ከታማኝ ምንጭ የተገኘው መረጃ ያስረዳል።


