የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አምስት ከፍተኛ አመራሮች
ላይ ተጥሎ የነበረው የውጪ ጉዞ ዕገዳ በይፋ ተነስቷል።
ጉዳዩን ከያዙት ጠበቆች በተገኘ መረጃ የፌዴሬል ከፍተኛ ፍ/ቤት ከፌዴራል ፖሊስ የቀረበለትን ጥያቄ ተመልክቶ ፕሬዝዳንቱ ዶክተር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ ፣ ዋና ጸሃፊው አቶ ዳዊት አስፋውና ምክትላቸው አቶ ገዛኧኝ ወልዴ፣ ሀቃቤ ነዋይዋ ኤደን አሸናፊ እንዲሁም የፓሪስ ኦሎምፒክ የቴክኒክና የህዝብ ግንኙነት ኮሚቴ ሃላፊ አቶ ቢልልኝ መቆያ ላይ የጉዞ ዕገዳ ሲጥል የተከሳሽ ጠበቆች ቅሬታ ያቀርባሉ።
ፍርድ ቤቱ ዶክተር አሸብር የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል በመሆናቸው ያለመከሰስ መብት ያላቸው በመሆኑ እንዲሁም የአፍሪካ ፓርላማ ም/ል አፈጉባኤ መህናቸውን ከግምት አስገብቶ እገዳውን በማንሳት የአራቱን አመራሮች ዕገዳ ማጽናቱ ጉዳዩን የያዙት ጠበቆችን ለፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ እንዲጠይቁ አድርጓል። ይግባኙ ውሳኔ ሳያገኝ በመሀል ወደ ውጪ ጉዞ ሊያደርጉ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ የደረሱ አንድ የኦሎምፒክ ኮሚቴው ከፍተኛ አመራር እንዲመለሱ የተደረጉ መሆኑ ይታወሳል።

- ማሰታውቂያ -
ዛሬ የቀረበለትን ይግባኝ የተመለከተው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰጠው ውሳኔ የአምስቱን የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ከፍተኛ አመራሮችን የውጪ ጉዞ እገዳ ሙሉ በሙሉ በማንሳት የከፍተኛ ፍርድ ቤቱን ውሳኔ መሻሩን እስታውቋል።


