በ45ኛው የለንደን ማራቶን የሴቶች ውድድር አትሌት ትዕግስት አሰፋ በ2:15:50 በቀዳሚነት አጠናቃለች።
አትሌቷ ውድድሩን ያጠናቀቀችበት ሰዓት ከፓውላ ራድክሊፍ 2:15:25 በመቀጠል የለንደን ማራቶን ሁለተኛው ፈጣን ሰዓት ሆኖ ተመዝግቧል።
በተጨማሪም የማራቶን የሴቶች ብቻ ክብረወሰንን በ26 ሰከንዶች በማሻሻል አዲስ ባለ ክብረወሰን ሆናለች።
ትዕግስት ከደራርቱ ቱሉ ፣ አሰለፈች መርጊያ ፣ ትዕግሥት ቱፋ እና ያለምዘርፍ የኋላው ቀጥሎ በለንደን ማራቶን ያሸነፈች 5ኛ ኢትዮጵያዊት አትሌት ሆናለች።
- ማሰታውቂያ -
ትዕግስት አሰፋ በአምናው ውድድር ፔሬስ ጄፕቼርቺርን በመከተል በሁለተኝነት አጠናቃ እንደነበርም ይታወሳል።
ኬንያዊቷ ጆይስሊን ጄፕኮስጌይ(2:18:44) እና ኔዘርላንዳዊቷ ሲፋን ሀሰን(2:19:00) የሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል።
አትሌት ሀቨን ሀይሉ በ2:19:17 የግሏን ምርጥ ሰዓት በማስመዝገብ በአራተኝነት አጠናቃለች።
በወንዶቹ ውድድር ደግሞ ኬንያዊው ሰባስትያን ሳዌ በ2:02:27 በቀዳሚነት ያጠናቀቀ ሲሆን ጃኮብ ኪፕሊሞ(2:03:37) እና እና አሌክሳንደር ሙቲሶ(2:04:20) የሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል።
የኦሊምፒክ ሻምፒዮኑ ታምራቶ ቶላ በ2:04:42 በአምስተኝነት ያጠናቀቀ ሲሆን አንጋፋው ኤሉድ ኪፕቾጌ በ2:05:25 በአምስተኝነት አጠናቋል።


