*… ለዕገዳው በዳኝነት ዘመናቸው ለመብታቸው ሲከራከርላቸው የነበሩት ዳኞች ከፍተኛ ድርሻ አላቸው…
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን
ብሄራዊ የዳኞች ኮሚቴ ኮሚሽነር ሚካኤል አርአያን በዓባይ ቲቪ የሜዳሊያ ፕሮግራም ላይ የሰጠውን አስተያየት በመቃወም ህጋዊ ርምጃ እንዲወሰድበት ጉዳዩን ለዲሲፕሊን ኮሚቴ መርቷል።
የፌዴሬሽኑ ጽ/ቤትም የኮሚቴውን ውሳኔ በመጥቀስ በጻፈው ደብዳቤ የብሄራዊ ዳኞች ኮሚቴ ክሱን ወደ ዲሲፕሊን ኮሚቴ የመራው በመሆኑ ዲሲፕሊን ኮሚቴ እስኪወስን ድረስ ኮሚሽነር ሚካኤል ከማንኛውም ምደባ መታገዱን አስታውቋል።
ብሄራዊ ዳኞች ኮሚቴ ባልተለመደ
መልኩ ባለሙያው ዓባይ ቲቪ ላይ የሰጠው ቃለምልልስ ” የተቋሙን ስም” በመተቸት በሚል ያቀረበው ቅሬታ ያለሃላፊነታቸው በማይመለከታቸው ስራ ገብተው ያቀረቡት ጥያቄ ቢሆንም የኮሚቴውን ውሳኔ ወደ ዲሲፕሊን ኮሚቴ መምራቱ የደረሰን መረጃ ያስረዳል።
- ማሰታውቂያ -
የውስጥ ሚስጢር መጠበቅ ባልቻሉ ወገኖች በቅድሚያ ማዕተም አልባ የሆነ የእገዳ ደብዳቤ የደረሰው ባለሙያው ያቀረበውን ቅሬታ በመቀበል ክልከላውን ያነሳው
ጽ/ቤቱ የዳኛ ኮሚቴ አባላትን ከሀዋሳ በአውሮፕላን እንዲመጡና እንዲወያዩ ያደረገው ሙከራ ኮሚሽነሩን ለመክሰስ ህጋዊ ድጋፍ እንዲያገኙ ከማስቻል ውጪ ምንም አለመፈየዱ አነጋጋሪ ሆኗል።
ሙሉ የዳኞች ኮሚቴ ከኮሚሽነር ሚካኤል አርአያ ጋር ውይይት ሲያደርጉ እናንተ ተቋሙን አትመሩም ተቋሙ ከተነካ ጽ/ቤቱ፣ ስራ አስፈጻሚና ፕሬዝዳንቱ እንጂ የዳኛ ኮሚቴ አያገባወም የሚለው የአካሄድ ጥያቄ በኮሚቴው አባል ህገወጥ የሞባይል ምስል ቀረጻ መታጀቡ የኮሚቴው አባላት ኮሚሽነሩ ላይ ምን ያህል ጥርስ እንደነከሱ የሚያሳይ ሆኗል። ኮሚሽነር ሚካኤል የዳኞቹ ማህበርን በምክትል ፕሬዝዳንትነት
እየመራ ለመብታቸው ሲታገልላቸው የነበሩ ዳኞች ጊዜ አግኝተው ኮሚቴ ሆነው ከሱ በተቃራኒ መቆማቸው እንደገረመው ለአባላቱ መግለጹ በርካታ ዳኞችን አሳዝኗል።
ጽ/ቤቱ አስቀድሞ የሰጠው መልስን ተከትሎ ኮሚሽነር ሚካኤል እንደገና ምላሹን አለመቀበሉን በመግለጽ ፍትህ የጠየቀበት ደብዳቤ ምላሽ ሳይሰጥ የኮሚቴው ውሳኔ መቅደሙ ባለሙያውን አስከፍቷል።
የውድድር ኮሚቴው ለኢትዮጵያ ዋንጫ በኮሚሽነርነት መድቦት ትላንት ወደ ሀዋሳ ለመሄድ እየተዘጋጀ የነበረው ባለሙያውን ማገዱ ውድድር ኮሚቴውና ብሄራዊ ዳኞች ኮሚቴ መሃል ያለውን ክፍተት ያሳየ ሆኗል።
በዓባይ ቲቪ የሜዳሊያ ፕሮግራም ላይ የኮሚቴው የአሰራር ችግሮችን እንዲስተካከል ከመግለጽ ውጪ አንድም ጊዜ ተቋሙንና አመራሮቹ ላይ የስም ማጥፋት ያልፈጸመው ኮሚሽነሩ በመናገር መብቱ ዙሪያ ለምን ህጋዊ ከለላ እንዳልተደረገለት የታወቀ ነገር የለም።
ትላንት ምሽት በተገኘ መረጃ የፌዴሬሽኑ የዲሲፕሊን ኮሚቴ በሰባት ቀን ውስጥ ለቀረበለት ክስ ምላሽ እንዲሰጥ ለኮሚሽነር ሚካኤል አርአያ በደብዳቤ መጠየቁ ታውቋል።


