የኢትዮጵያ እድሜያቸው ከ20 ዓመት በታች /U-20/ ወንዶች ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ግንቦት 29 ቀን 2008 ከማሊ አቻው ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ለማድረግ ትናንት ግንቦት 28/2008 ወደ ቦታው ተጉዞ ማረፊያውን ኮሎምቦስ ሆቴል አድርጎል።
ማምሻውን በማማኮ ከተማ ልምምዱን በማድረግ ዛሬ ቀን የነፃነት ታጋይ በነበሩት ስም በተሰየመው ማዲቦ ኬይታ ብሔራዊ ስታዲየም በአገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር 11:00 ሰዓት ሲሆን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ በ2:00 ሰዓት ጨዋታውን ያካሂዳል።
ድል ለብሔራዊ ቡድናችን::

አስተያየት ይስጡ