በኢትዮጵያ ዋንጫ የሩብ ፍፃሜ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ መቐለ 70 እንደርታ የከፍተኛ ሊጉን ቦዲቲ ከተማን 3ለ2 በመርታት ወደ ግማሽ ፍፃሜው አልፏል።

ዘጠኝ ሰዓት ሲል በአዲስ አበባ ስታዲየም በኢትዮጵያ ዋንጫ የሩብ ፍፃሜ የመጀመሪያ ቀን መርሀግብር የፕሪምየር ሊጉን ክለብ መቐለ 70 እንደርታን በከፍተኛ ሊጉ ምድብ ለ ላለመውረድ እየታገለ ካለው ቦዲቲ ከተማ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 3ለ2 በመርታት ወደ ግማሽ ፍፃሜውን መሸጋገር ችሏል። ቦዲቲዎች 25ኛው ደቂቃ ከግራ የማዕዘን ምት የተሻማች ኳስን በትዕዛዙ መንግሱ ሞክራ በግቡ ቋሚ ስትመለስ ሙሉቀን ተስፋዬ ወደ ጎልነት ለውጦ የአሰልጣኝ አዲሱ ዶይሶን ክለብ መሪ ማድረግ ችሏል። ግብ ካስተናገዱ በኋላ አቻ ለመሆን ጥረት ያደረጉት መቐለዎች 37ኛው ደቂቃ በጨዋታው የጎመራው ፍፁም አለሙ በጥልቀት ከቦና አሊ ጋር በነበረው ጥምረት የቦዲቲ ተከላካዮች ስህተት ታክሎበት ሞዓም አናብስቱን አቻ አድርጓል።

ከዕረፍት መልስ በይበልጥ በቆሙ እና በሽግግር ከሚነሱ ኳሶች ማጥቃታቸውን አጠናክረው የቀጠሉት መቐለዎች 71ኛው ደቂቃ ከፍፁም አለሙ መነሻዋን አድርጋ በተከላካይ እና በግብ ጠባቂ ተነካክታ የተመለሰችን ኳስ አዲሱ የክለቡ ፈራሚ ፕሪንስ ኦፊሬ የመሪነት ጎል አድርጓታል ከደቂቃዎች በኋላ ቦና አሊ ሦስተኛዋን ጎል ከመረብ ሲያሳርፍ ጨዋታው ሊጠናቀቅ በመጨረሻዎቹ አምስት ደቂቃዎች መነቃቃት የጀመሩት ቦዲቲዎች በቴዎድሮስ በለጠ አማካኝነት ጎል ቢያገኙም ከሽንፈት ማዳን ሳትችል ጨዋታው 3ለ2 የመቐለ አሸናፊነት መቋጨት ችሏል። መቐለም በግማሽ ፍፃሜው ከኢትዮጵያ መድን እና ቤንች ማጂ አሸናፊ ጋር ለፍፃሜ ለማለፍ ይፋለማል።

የኢትዮጵያ ዋንጫ ቀጣይ መርሀግብር ነገም ሲቀጥል መቻል ከ ወልዋሎ ዕርብ ኢትዮጵያ መድን ከቤንች ማጂ ቡና ቅዳሜ ደግሞ ነገሌ አርሲ ከ ሲዳማ ቡና ጋር ይፋለማሉ።
አስተያየት ይስጡ