መነሻ ገጽ Uncategorized ወልዋሎ ወደ ግማሽ ፍፃሜው ማለፉን አረጋገጠ
Uncategorized

ወልዋሎ ወደ ግማሽ ፍፃሜው ማለፉን አረጋገጠ

አጋራ
አጋራ

በኢትዮጵያ ዋንጫ የሩብ ፍፃሜ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ወልዋሎ ዓ/ት ዩኒቨርስቲ በመለያ ምት መቻልን በመርታት ወደ ግማሽ ፍፃሜው ያለፈ ሁለተኛው ክለብ ሆኗል።

ትላንት መቐለን ወደ ግማሽ ፍፃሜው በማሳለፍ ጅምሩን ያደረገው የኢትዮጵያ ዋንጫ መርሀግብር በሁለተኛ ቀኑ ዛሬም ቀጥሎ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርስቲን ከመቻል ያገናኘ ነበር። መቻሎች በብዙ ረገድ በሁለቱም አጋማሾች በተሻለ ለመጫወት ጥረት ባደረጉበት ጨዋታ የሚያገኟቸውን ዕድሎች መጠቀም ባለመቻላቸው በመጨረሻም ለሽንፈት ተዳርገዋል።

በጨዋታው መጠናቀቂያ ላይ አምበሉ እና አማካዩን ፍሬው ሠለሞንን በሁለት ቢጫ ካርድ ለማጣት የተገደዱት ወልዋሎዎች ጨዋታው ያለ ጎል መጠናቀቁን ተከትሎ በተሰጠው የመለያ ምት በዩጋንዳዊው የግብ ዘብ ሙታክብዋ ጆኤል አስደናቂ ብቃት ታግዘው 5ለ4 በሆነ ውጤት አሸንፈው ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍ ችለዋል።

ነገ ጨዋታው ሲቀጥል የከፍተኛ ሊጉ ቤንች ማጂ ቡና ከኢትዮጵያ መድን ቅዳሜ ደግሞ ነገሌ አርሲን ከ ሲዳማ ቡና ያገናኛል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
Uncategorized

FIFA temporarily lifts transfer ban on St. George

Saint George's has had its transfer ban imposed by FIFA temporarily lifted...

Uncategorized

29ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ዳግም ወንድሙ (ሀዲያ ሆሳዕና) : ክለቡ ከ መቐለ 70 እንደርታ...

Uncategorized

ሀይለየሱስ ባዘዘው ከዳኝነት አለም ራሳቸውን አገለሉ

ሀያ አምስት አመታቶችን በዳኝነት ያገለገሉት ዶ/ር ሀይለየሱስ ባዘዘው ከዳኝነት አለም በይፋ ማቆማቸውን...

Uncategorized

በኢትዮጵያ ዋንጫ መቐለ ወደ ግማሽ ፍፃሜው ተሻግሯል

በኢትዮጵያ ዋንጫ የሩብ ፍፃሜ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ መቐለ 70 እንደርታ የከፍተኛ ሊጉን...