መነሻ ገጽ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሚጀመርበት ቀን ተራዘመ
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሚጀመርበት ቀን ተራዘመ

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሚጀመርበት ቀን ለአንድ ሳምንት መራዘሙን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ገለጸ።የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ጨዋታ ፕሮግራም ደግሞ ወደ ጥቅምት ሰባት መራዘሙን ፌደሬሽኑ አስታውቋል።

የፌዴሬሽኑ የውደድርና ተሳትፎ ኃላፊ አቶ ሰለሞን ገብረስላሴ ለኢዜአ እንደገለጹት ሊጉ የሚጀመርበት ቀን ሊራዘም የቻለው የአዲስ አበባ ስታዲየም ጭቃ በመሆኑ ውድድር ማስተናገድ ስለማይችልና ሌሎች የሲቲ ካፕ ውድድሮች በመኖራቸው ነው።
የሲቲ ካፕ ውድድሮች በደቡብ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽንና በአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት የሚደረጉ ናቸው።
በእነዚህ ምክንያቶች ሊጉ ከጥቅምት አራት ወደ ጥቅምት አስራ አንድ መራዘሙን አቶ ሰለሞን ተናግረዋል።
መስከረም 27 ለማካሄድ ቀጠሮ የተያዘለት የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር ጥቅምት ሰባት እንዲካሄድ ተወስኗል።
በ1990 ዓም በአዲስ መልክ የተጀመረው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በአስራ ስድስት ክለቦች መካከል የሚደረግ ነው።
ምንጭ -ኢዜአ

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበርየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በኣትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለዋጭ ስህተት ሰርቷል የተባለውን ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

አሰልጣኝ ኤርሚያስ በቀለ እግርኳስ ፌዴሬሽኑን ከሰሰ…

አሰልጣኝ ኤርሚያስ በቀለ /ሮማሪዮ/ መብቴን ጥሷል ያለውን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽንን በመደበኛ ፍርድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበርየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ብሄራዊ  ዳኞች ኮሚቴ ዳኞችን የለየ ውሳኔን አሳልፈዋል

ኢንተርናሽናል አርቢትር ባህሩ ተካን በማሰናበት ኢንተርናሽናል አርቢትር ቴዎድሮስ ምትኩን ባላየ ማለፉ አነጋጋሪ ሆኗል። ብሄራዊ...