መነሻ ገጽ Uncategorized ኢትዮጵያ ውሃ ስራ የአማራ ውሃ ስራውን አሰልጣኝ ደግአረግ ይግዛውን በኃላፊነት ሾሟል
Uncategorized

ኢትዮጵያ ውሃ ስራ የአማራ ውሃ ስራውን አሰልጣኝ ደግአረግ ይግዛውን በኃላፊነት ሾሟል

አጋራ
አጋራ

 

ኢትዮጵያ ውሃ ስራ የአማራ ውሃ ስራውን አሰልጣኝ ደግአረግ ይግዛውን በኃላፊነት ሾሟል::
-አቶ አበባው ከልካይ ስራ አስኪያጅ ሆነው ተቀጥረዋል
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ተወዳዳሪ የነበረውን የአማራ ክልል ተወካይ አማራ ውሃ ስራን ላለፉት ጥቂት ዓመታት ያሰለጠነው አሰልጣኝ ደግአረግ ይግዛው በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ውሃ ስራን ለመጪዎቹ ሁለት ዓመታት ለማሰልጠን በኃላፊነት ተሾሟል፤ የአሰልጣኝነትU ሕይወት ውስጥ ከአማራ ውሃ ስራ ባሻገር በሌሎች ክለቦችም በመስራት የሚታወቀው አሰልጣኝ ደግአረግ የአማራ ስራ ጋር ውሉን በማራዘም ይቀጥላል ተብሎ ቢጠበቅም አዲሱን ክለብ በይፋ ተቀላቅሏል፡፡
የኢትዮጵያ ውሃ ስራን ኃላፊነት በመረከብ ፊርማውን ማኖር የቻለው ደግአረግ ከአሰልጣኝነቱ በተጨማሪ  በተጨዋችነት ዘመኑ በአሁን ሰዓት በሕይወት በሌሉት በአሰልጣኝ እና ኢንስትራክተር በነበሩት ታዋቂው የሀገራችን እግር ኳስ ተጨዋች መንግስቱ ወርቁ በመመልመል ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር በ1981 መጨረሻ ላይ የክለቡን የዝግጅት ጊዜ እና የአቋም መለኪያ ጨዋታዎች ላይ በመቀላቀል ቆይታ አድርጎ የነበረ ሲሆን ከእዚያ ባሻገር በኢንስትራክተር ካሳሁን ተካ በሚመራው የባህር ኃይል እና በአሰልጣኝ አስራት ኃይሌ በሚመራው የጉምሩክ ቡድን ውስጥም ተጫውቶ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ላይ በዘንድሮ የውድድር ዘመን በምድብ አንድ የተደለደለውን የአማራ ውሃ ስራን በአሰልጣኝነት በመምራት ያሳለፈው ደግአረግ ከምድቡ ባደረጋቸው 30 ጨዋታዎች ምድቡን በ4ኛነት በማጠናቀቅ ወደ ፕሪምየር ሊጉ ለማለፍ ለጥቂት እድሉ ያመለጠው ሲሆን የመጪው ዓመት ላይ አዲሱን ክለቡ በማሰልጠን ወደፕሪምየር ሊጉ ለማለፍ ሌላኛውን ዕድሉን የሚሞክርም ይሆናል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ ውሃ ስራ የቀድሞ ስራ አስኪያጁን አሸናፊ እጅጉን ከኃላፊነት ካነሳ በኋላ አዲስ ስራ አስኪያጅ ቀጥሯል፤ ወደ ውሃ ስራ የገቡት አዲሱ ስራ አስኪያጅም ቀደም ሲል በነበሩት ዓመታት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ውስጥ እና በሚንስትር መስሪያ ቤት ውስጥ ከፍተኛ ቦታ ላይ ሲሰሩ የነበሩት አቶ አበባው ከልካይ ናቸው፡፡ ከእነሱ ባሻገር ክለቡ ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የመጣውን ዳንኤል የተባለ ቴክኒካል ዳይሪክተር መቅጠሩም ተሰምቷል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
Uncategorized

ቅዱስ ጊዮርጊስ የመቶ ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገለት

ዛሬ አንጋፋውን የቅዱስ ጊዮርጊስ የስፓርት ማህበር ከገጠመው የመፍረስ አደጋ ለመታደግ የተለያዩ አካላትን...

Uncategorized

ለዋልያዎቹ መጫወትን የሚመኘው የሴሪ ኣው ክለብ ተጫዋች ማነው ?

የጣሊያን ሴሪ ኣው ክለብ ቶሪኖ ንብረት ስለሆነው አስደናቂው የአጥቂ አማካይ ተጫዋች እንንገራችሁ።...

Uncategorized

ቡናማዎቹ ተጫዋች ለማስፈረም ተስማሙ !

  በዛሬው ዕለት ግብ ጠባቂ በማስፈረም ወደ ዝውውሩ የገቡት ኢትዮጵያ ቡናማዎች ዘካሪያስ...