በኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ የምድቡ አሸናፊ እንዲሁም በማጠቃለያ ውድድር ላይ 2ኛ ደረጃን ይዞ ላጠናቀቀው የደሴ ከነማ እግር ኳስ ክለብ ልኡካን ቡድን፤ተጋባዥ እንግዶችና ደጋፊዎችን ጨምሮ የእራት ግብዣ ኘሮግራም ትናንት ምሽት ተዘጋጅቶ ነበር፡፡
በዚሁ ዝግጅት ላይ ቃል የተገባላቸዉን 600ሺ ብር ወጭ በማድረግ ለክለቡ ውጤት አስተዋፅኦ ለነበራቸው አካላት ለእያንዳንዳቸው የገንዘብ ሽልማት ተሠጥቷል፡፡
1.ለክለቡ ዋና አሠልጣኝ 30ሺ ብር
2.ለክለቡ ምክትል አሠልጣኝ 20ሺ ብር
3.ለ1ኛ ደረጃ ተጨዋቾች 20ሺ ብር
4.ለ2ኛ ደረጃ ተጨዋቾች 15 ሺ ብር
5.ለ3ኛ ደረጃ ተጨዋቾች 10 ሺ ብር
6.ለ4ኛ ደረጃ ተጨዋቾች 8 ሺ ብር የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡
ከዚህ በተማሪም ለተጨዋቾች ምግብ የሚያበስሉ፤የፅዳት አገልግሎት የሚሠጡ፤ሾፌር፤ወጌሻ ገንዘብ ያዥን ጨምሮ ለበርካቶች ሽልማት ተበርክቷል፡፡
አመቱን ሙሉ ክለቡን በተለያዬ መንገድ ሲያበረታቱ ለነበሩ ቀንደኛ የክለቡ ደጋፊዎችም የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል ፡፡
በቀጣይ የከፍተኛ ሊጉን ዉድድር በድል ከተወጡ ዳጎስ ያለ ሽልማት እንደሚጠብቃቸው ቃል ተገብቷል፡፡
source-dessie kenema official fb page
አስተያየት ይስጡ