መነሻ ገጽ ዜናዎች በአንደኛ ሊግ ትላንት የነበረውን አስቀያሚ ነገር እንንገራችሁ
ዜናዎችየኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ

በአንደኛ ሊግ ትላንት የነበረውን አስቀያሚ ነገር እንንገራችሁ

አጋራ
አጋራ

በሁለተኛው ዙር ጠብ በማያጣው የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ ትላንት በምድብ ሀ ረፋድ ላይ የነበረው ምንድነው ?

የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ የምድብ ሀ ጨዋታዎች በቢሾፍቱ ከተማ እየተደረገ ይገኛል። ወደ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የሚያድጉ ቡድኖችን ለመለየት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን በሚዘጋጀው በዚህ ውድድር ላይ ትላንት በኮንሶ ኒውዮርክ እና ኑዌር ዞንን አገናኝቶ የነበረው ጨዋታ ከተጠናቀቀ በኋላ መጨረሻው ሳያምር አምስት ተጫዋቾች ወደ ሆስፒታል ያመሩበት ክስተት ተፈጥሯል።

በሁለተኛው ዙር ተመሳሳይ ድርጊቶችን እያስተናገደ እንዳለ የሚነገርለት ይህ ውድድር ትላንት ዕሁድ ጠዋት 3 ሰዓት ሲል ቢሾፍቱ ስታዲየም ላይ የሁለቱ ቡድን ጨዋታ መደረግ የቻለ ሲሆን በመጀመሪያው አጋማሽ ኑዌር ዞኖች ጎል አስቆጥረው እየመሩ ወደ መልበሻ ክፍል ያመሩ ሲሆን ከዕረፍት በኋላ ገና በአንደኛው ደቂቃ ኮንሶ ኒውዮርኮች ጎል አስቆጥረው ጨዋታው 1ለ1 በሆነ ውጤት በመጨረሻም ፍፃሜውን አግኝቷል።

ጨዋታው በሰላም ከተጠናቀቀ በኋላ በተጫዋቾች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት ወደ መኪናቸው ሲያመሩ በነበሩ የኮንሶ ኒውዮርክ ተጫዋቾች እና የመኪናው ሾፌር እና ረዳት ላይ ከፍተኛ ጉዳይ ደርሶ ወደ ሆስፒታል አምርተው ህክምና የተደረገላቸው ሲሆን ባደረግነው የመረጃ ማሰባሰብ ስራ የኑዌር አሰልጣኝ እና የቡድኑ ተጫዋቾች የፈጠሩት አላስፈላጊ ድርጊት ለጠቡ መነሻ እንደሆነ ሰምተናል። ሀገራችን ኢትዮጵያ በላቀ ደረጃ እግር ኳሷ አድጎ ነገ የተሻለ ማየትን ብንመኝም እንዲህ አይነት አስነዋሪ በድንጋይ እና ቦክስ የተነሳ የማይሆን ቦታ ላይ ሆኖ ማየታችን እጅጉን ያቆስላል።

በመጨረሻም ይህ ጥል የከፋ ደረጃ ላይ እንዳይደርስ የቢሾፍቱ እግር ኳስ ወዳድ ህዝብ መመስገን እንዳለበት መረጃ ያደረሱን በጠቅላላ ነግረውናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ሲዳማ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የሲዳማ ቡና ቡድን መሪ ታገደ

በዮሴፍ ከፈለኝ የፕሪምየር ሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና የቡድን መሪው የቀድሞው ዳኛ ዕግድ...

ዜናዎችየዲሲፕሊን ውሳኔዎች

27ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አብዱላጢፍ ባምባ (መቐለ 70 እንደርታ) : ክለቡ ከ ወልዋሎ አዲግራት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...