መነሻ ገጽ ዜናዎች አሰልጣኝ ጳውሎስ (ማንጎ) ከአምስት ጨዋታዎች በኋላ ተሰናበቱ
ዜናዎችየኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ

አሰልጣኝ ጳውሎስ (ማንጎ) ከአምስት ጨዋታዎች በኋላ ተሰናበቱ

አጋራ
አጋራ

አዲስ የተቀጠሩት እና ዛሬ ቡድኑን የመሩት አሰልጣኝ መሳይ በየነ ቡድኑን በአንድ ጨዋታ ከወራጅ አውጥተውታል።

ሐረር ከተማን በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ላይ ምድብ ሀ በሊጉ እንዲያቆዩ ተቀጥረው በሁለተኛው ዙር አምስት ጨዋታዎች የመሩት ሐረር ከተማዎች አሰልጣኝ ጳውሎስ ጌታቸው (ማንጎን) በማሰናበት በምትኩም የቀድሞው የቡታጂራ እና ቡራዩ ከተማ አሰልጣኝ የሆኑት መሳይ በየነ ተረክበዋል። የቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና ፣ ባህርዳር ከተማ ፣ ሀድያ ሆሳዕና ፣ ጅማ አባጅፋር እና አዲስ አበባ ከተማ አሰልጣኝ የነበሩት አሰልጣኝ ጳውሎስ ክለቡን ለማትረፍ በሁለተኛው ዙር እስማኤል አቡበከርን ተክተው ቡድኑን ቢረከቡም በውጤት መጥፋት እና በሌሎች ሚስጥር ናቸው በተባልኩት ጉዳዮች ተካተውበት ከአሰልጣኝነት ተሰናብተዋል።

ዛሬ ቡድኑን የተረከቡት አሰልጣኝ መሳይ በየነ በመጀመሪያ ጨዋታቸው ነቀምት ከተማን 3ለ1 በማሸነፍ ከወራጅ ቀጠናው ግርጌ በመውጣት በ10 ነጥቦች 8 ደረጃ ላይ መቀመጥ የቻለ ሲሆን በምትኩ አቃቂ ቃሊቲ ወደ ወራጅ ገብቷል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...