መነሻ ገጽ ኢትዮጵያን በውጪ በጀርመኑ ኑረን በርግ የሚገኘው የ18 አመቱ የአጥቂ አማካይ
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

በጀርመኑ ኑረን በርግ የሚገኘው የ18 አመቱ የአጥቂ አማካይ

አጋራ
አጋራ

ከኢትዮጵያዊ አባት የተገኘውን አማካይ ይዘንላችሁ ቀርበናል።

አባቱ ኢትዮጵያዊ ሲሆን እርሱ የተወለደው ግን በጀርመን ነው። ሞግል ዶርፍ ከተባለ የእግር ኳስ ማሰልጠኛ የተገኘው በአሁኑ ሰዓት ዕድሜው 18 የደረሰው የአጥቂ አማካዩ ኪሩቤል ታዬ። እግር ኳስን አቅልለው ከሚጫወቱ ተጫዋቾች መካከል አንዱ እንደሆነ የሚነገርለት ይህ ተጫዋች በጀርመን ቡንደስሊጋ ተሳታፊ በነበረው እና በአሁኑ ሰዓት በጀርመን ሁለተኛ ሊግ ላይ በሚገኘው ኑረን በርግ ወጣት ቡድን ከ2016 ጀምሮ በመጫወት ላይ የሚገኝ ሲሆን በቡድኑ ከ17 አመት በታች ቡድን ውስጥ ከተጫወተ በኋላ በመቀጠልም ከሁለት አመት በፊት ጀምሮ ደግሞ በዛው በኑረን በርግ ከ19 አመት በታች ቡድን ይገኛል።

በጀርመን ከ19 አመት በታች ፕሪምየር ሊግ እንዲሁም በሌሎች መድረኮች ለኑረን በርግ በሀያ ጨዋታዎች ተሰልፎ ለአንድ ሺህ አምስት መቶ ስልሳ አራት ደቂቃዎች ክለቡን በማገልገል በድምሩ 2 ጎሎችን ያስቆጠረው ተጫዋቹ በቀጣይ ክረምት የኑረን በርግን ዋናውን ቡድን እንደሚቀላቀል የሚጠበቅ ሲሆን የአባቱን ሀገር ኢትዮጵያን ደግሞ በብሔራዊ ቡድን መወከል እንደሚፈለግ ይናገራል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያ ቡናዜናዎችየዝውውር ዜናዎች

ኢትዮጵያ ቡና ግብ ጠባቂ አስፈረመ

መሳይ አያኖ አዲሱ የኢትዮጵያ ቡና የግብ ዘብ ሆኗል። በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የሚሳተፈው...

ሲዳማ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የሲዳማ ቡና ቡድን መሪ ታገደ

በዮሴፍ ከፈለኝ የፕሪምየር ሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና የቡድን መሪው የቀድሞው ዳኛ ዕግድ...

ዜናዎችየዲሲፕሊን ውሳኔዎች

27ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አብዱላጢፍ ባምባ (መቐለ 70 እንደርታ) : ክለቡ ከ ወልዋሎ አዲግራት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...