ከኢትዮጵያዊ አባቱ የተገኘውን ሀገራችንን የማገልገል ፍላጎት ያለው አማካይ ማነው ?

አባቱ ኢትዮጵያዊ ሲሆኑ ካሳ ጋቶ ይባላሉ። የዛሬው ፅሁፌ የሚያውጠነጥነው ልጃቸው ደግሞ የተወለደው እስራኤል ውስጥ ሲሆን ስሙም ሊዮር ካሳ እየተባለ ይጠራል። በአሁኑ ሰዓት ሀያ አመቱ ላይ የደረሰው እና አንድ ሜትር ከሰማንያ አምስት ሴንቲ ሜትር ርዝማኔ ያለው ይህ የአጥቂ አማካይ ስፍራ ተጫዋች እግር ኳስን በእስራኤል ፕሪምየር ሊግ በሚሳተፈው ሀፖል ጄሩሳሌም ውስጥ ሲሆን በነበረው አስደናቂ እንቅስቃሴም ወደ ጣሊያን ሴሪያው ክለብ ጄንዋ በማምራትም በክለቡ ጥሩ ጊዜን አሳልፏል።


እስራኤልን በአለም ዋንጫ እና በአውሮፓ ውድድሮች ላይ ከ17 ፣ ከ18 ፣ ከ19 እና ከ21 አመት በታች ቡድኖቿን በሚገባ ያገለገለው ይህ ተጫዋች ባለፈው አመት ወደ እስራኤል ተመልሶ ለማካቢ ሀይፋ እስከ 2028 በመፈረም ቡድኑን በአውሮፓ ኮንፍረንስ ሊግ ጭምር ማገልገል ችሏል። ኢትዮጵያን በትልቁ ብሔራዊ ቡድኗ ውስጥ ተጠርቶ ማገልገል ቀጣዩ ህልሙ እንደሆነ አማካዩ ፍላጎቱን በአንድ ቃለ መጠይቅ ላይ ሲናገር ተደምጧል።
አስተያየት ይስጡ