መነሻ ገጽ ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣ ሰበር ዜና፡-ሰመራ ላይ ታህሳስ 16 ይካሄዳል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ጠ/ጉባኤና ምርጫ ጥር 5 እንዲካሄድ አስመራጭ ኮሚቴው ወሰነ
ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንጠቅላላ ጉባዔ

ሰበር ዜና፡-ሰመራ ላይ ታህሳስ 16 ይካሄዳል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ጠ/ጉባኤና ምርጫ ጥር 5 እንዲካሄድ አስመራጭ ኮሚቴው ወሰነ

አጋራ
አጋራ

ህዳር 14 ቀን የተቋቋመው አስመራጭ ኮሚቴ በትናንትናው ዕለት የብዙሃኑን የሚዲያ እካላት ጥያቄ ያልመለሰ የይስሙላ ጋዜጣዊ መግለጫ በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል መስጠቱ ይታወሳል።
በርካታ የህግ ጥሰቶችን ፈፅሞ በሚዲያዎች ፊት የቀረበው አስመራጭ ኮሚቴው ከሚዲያ አካላት ለቀረቡት በርካታ ኮርኳሪና አንገብጋቢ የህዝብ ጥያቄዎች በመድረኩ መሪዎች አቅም ማነስና ሽፋፋኝነት በቂና አሳማኝ ምላሽ ሳያገኝ ነው ይተጠናቀቀው።
በበርካታ የህግ ጥሰቶችና ህፀፆች የተሞላው አስመራጭ ኮሚቴው ሠመራ ላይ ይካሄዳል ተብሎ ለሚጠበቀው ምርጫ 5 ለፕሬዝዳንታዊ 16 ደግሞ ለስራ አስፈፃሚነት የሚወዳደሩ ዕጩዎችን ማንነት ቢያሳውቅም ጠቅላላ ጉባኤውና ምርጫው በተያዘለት ቀን ታህሳስ 16 ይካሄዳል?የሚለው ቁርጥ ያለ ምላሽ ሣያገኝ ቆይቷል።
ሀትሪክ ከደቂቃዎች በፊት ባገኘችው የተረጋገጠ መረጃ ሠመራ ላይ ታህሳስ 16 ቀን ይካሄዳል ተብሎ የሚጠበቀው ምርጫ ወደ ጥር 5 ቀን መዘዋወሩ ተረጋግጧል።
ፊፋ ምርጫ ለማካሄድ የያዛችሁት ቀን ታህሳስ 16 ቀን የፈረንጆች ገና የሚከበርበት በመሆኑ በጉባኤው ለመሳተፍ ስለምቸገር ምርጫችሁን ለ10 ቀናት እራዝሙ በማለት ደብዳቤ የላከ ሲሆን አስመራጭ ኮሚቴው በበኩሉ ፈረንጆች ገና ስንል አራዝመን የእኛስ?የሚል ጥያቄን በማስነሳቱ ምርጫው በ19 ተጨማሪ ቀናቶች ተራዝሞ ጥር 5 ቀን ሠመራ ላይ እንዲካሄድ አስመራጭ ኮሚቴው ያለ ልዩነት በሙሉ ድምፅ ወስኗል።ይሄንን ውሳኔ ተከትሎ በግርግሩ መሹለክ የፈለጉ ዕጩ ተወዳዳሪዎችና የስልጣን ጀምበራቸው የጠለቀችባቸው የግለሰብ አጀንዳን የሚያራምዱ የቀድሞ ስራ አስፈፃሚዎች እንዴት ይራዘማል? በሚል አስመራጭ ኮሚቴው ላይ የተለያዩ ጫናዎችን እያደረጉ ቢሆንም አስመራጭ ኮሚቴው ምርጫው ለ ጥር 5 መራዘሙን ለፈፋ አሳውቆ ፊፋም ውሳኔውን ስለመቀበሉና በምርጫው ዕለት ታዛቢ እንደሚልክ ማረጋገጫ መላኩም ታውቋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበርየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በኣትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለዋጭ ስህተት ሰርቷል የተባለውን ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

አሰልጣኝ ኤርሚያስ በቀለ እግርኳስ ፌዴሬሽኑን ከሰሰ…

አሰልጣኝ ኤርሚያስ በቀለ /ሮማሪዮ/ መብቴን ጥሷል ያለውን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽንን በመደበኛ ፍርድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበርየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ብሄራዊ  ዳኞች ኮሚቴ ዳኞችን የለየ ውሳኔን አሳልፈዋል

ኢንተርናሽናል አርቢትር ባህሩ ተካን በማሰናበት ኢንተርናሽናል አርቢትር ቴዎድሮስ ምትኩን ባላየ ማለፉ አነጋጋሪ ሆኗል። ብሄራዊ...