በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አራት ጨዋታ እየቀራቸው የሊጉን ሻምፒዮንነት ቀድመው ያረጋገጡትና ዋንጫውን ያነሱት አፄዎቹ ከኮከባቸው እንየው ካሳሁን ጋር ሊለያዩ ከጫፍ ደርሰዋል።
በሊጉ በቀኝ መስመር ተከላካይነት በግንባር ቀደምትነት ቡድኑን በማገልገል ከሚጠቀሱት ተጫዋቾች መካከል አንዱ የሆነው እንየው ካሳሁን ከአፄዎቹ ጋር በደሞዝ እና ጥቅማቅም ምክንያት ባለመስማማቱ ከሻምፒዮኖቹ ጋር የመቀጠሉ ነገር ጥያቄ ውስጥ ገብቷል።
ተጫዋቹ ከሀትሪክ ስፖርት ጋር በነበረው አጭር ቆይታ ከተለያዩ የሊጉ ክለቦች ዘንድ በርከት ያሉ ጥያቄዎች እየቀረቡለት እንደሆነ እና ከሚወደው ክለብ ግን የመልቀቅ ፍላጎት እንደሌለው ገልጿል ።
ተጨዋቹ ሲቀጥል ከፋሲል ከነማ በክለብ ደረጃ እና በፋይናንስ ከሚስተካከሉ እና ከሚያንሱ ቡድኖች የተሻለ የደሞዝ እና ጥቅማጥቅሞች እየቀረቡለት መሆኑ ግርምት እንደ ፈጠረበትም ተናግሯል ።
አስተያየት ይስጡ