ለ12 አመታት ያህል ለቅዱስ ጊዮርጊስ የተጫወተው ምንተስኖት አዳነ ለአዳማ ከተማን ለመጫወት ተስማምቷል። ከደቂቃዎች በፊት በተገኘ መረጃ ተጨዋቹ ለቀጣዮቹ 2 አመታት ለመጫወት ፊርማውን አኑሯል።
ተጨዋቹ ፈረሰኞቹን ከታዳጊ እስከ ዋናው ቡድን አምበልነት ያገለገለ ሲሆን 7 የፕሪሚየር ሊግ፣2 የአሸናፊዎች አሸናፊ፣2 የኢትዮዽያ ዋንጫን ጨምሮ ወደ 17 ዋንጫዎችን አሳክቷል። ሰኔ መጨረሻ ውሉ መጠናቀቁ ተከትሎ ጊዮርጊሶች ውሉን ባለማደሳቸው የቀድሞ አሰልጣኙ ፋሲል ተካልኝን ተከትሎ ወደ አዳማ ከተማ ማቅናቱ ተረጋግጧል።
አስተያየት ይስጡ