ባሳለፍነው እሁድ በመቐለ ዩኒቨርስቲ ኣስተናጋጅነት በደማቅ ስነ-ስርዓት የተከፈተው 9ኛው የመላ ኣፍሪካ ዩኒቨርስቲ ጨዋታዎች ትላንት በመቐለ ዩኒቨርስቲ ዓዲ ሓቂ ካምፓስ ላይ በተደረገ ያማረ የመዝግያ ስነ-ስርዓት ተጠናቋል።በመዝግያው ስነ-ስርዓት ከውስጥ እና ከውጭ ሃገር የተጋበዙ የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።
58 የኣፍሪካ ዩኒቨርስቲዎች በተሳተፋበት በዚህ ውድድር ከ ስፓርታዊ ውድድር ውጪ የባህልና የቴክኖሎጂ ልውውጦች የተካሄደበት ነበር።መቐለ ዩኒቨርሲቲም ኣፍሪካውያን በኣንድ መንደር የተሰባሰቡበትን ዝግጅት በሙሉ ብቃት ኣስተናግዳ ጨርሳለች።

NDDEJJE ዩኒቨርስቲ በኣጠቃላይ ውድድሩ ላይ በኣገኛቸው 10 ወርቅ፣4 ብር እና 5 ነሃስ በኣጠቃላይ 19 ሜዳልያዎች የውድድሩ ኣሸናፊ ሆኗል።ኢትዮጵያን ከወከሉ 11 ዩኒቨርስቲዎችም ኣዲስኣበባ ዩኒቨርስቲ ባገኛቸው 8 ወርቅ፣6 ብር እና 11 ነሃስ ሦስተኛ ደረጃን መያዝ ችሏል።

ብዙ ተመልካች የተከታተለው የወንዶች እግር ኳስ በዛንዚባር ዩኒቨርስቲ ኣሸናፊነት ተጠናቋል።በፍፃሜው ጨዋታ ኮተቤ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅን የገጠሙት ዛንዚባሮች ሦስት ለኣንድ በሆነ ውጤት በማሸነፍ ዋንጫውን ማንሳት ችለዋል።
የሃገራት የሜዳልያ ደረጃን ኡጋንዳ ኢትዮጵያ ና ጋና በቅደም ተከተል ከኣንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ በመያዝ ኣጠናቀዋል።


አስተያየት ይስጡ