አጋራ

በሀገሪቱ ተከስቶ በነበረዉ ጦርነት ምክንያት በፕሪሚየር ሊግ እና ከፍተኛ ሊግ በመሳሰሉ ዉድድሮች ላይ ተሳታፊ የነበሩት ክለቦች ከውድድር ዉጭ መሆናቸዉ የሚታወስ ሲሆን ፤ አሁን ላይ ግን በሀገሪቱ በተፈጠረው ሰላም መሰረት የትግራይ ክልል ክለቦች ወደ ዉድድር እንደሚለሱ የክልሉ እግርኳስ ፌደሬሽን ለሚመለከታቸዉ አካላት ጥያቄ አቅርቧል።

በዚህም መቀለ 70 እንደርታ ፣ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ እና ስሁል ሽሬን የመሳሰሉ በሊጉ ተሳታፊ የነበሩት ክለቦች እንዲሁም በሴቶች ፕሪምየር ሊግ ፣ብሔራዊ ሊግ እና ከፍተኛ ሊግ ተሳታፊ የነበሩ ወደ ዘጠኝ የሚደርሱ ክለቦች በጦርነቱ ምክነያት በደረሰባቸው ውድመት ምክንያት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን ፣ የኢትዮጵያ ባህል እና ስፖርት ሚኒስትር ፣ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ እና የኢትዮጵያ ስፖርት ኮሚሽን አስፈላጊዉን ድጋፍ አድርገዉላቸዉ በ2016 ወደ ውድድር እንዲመለሱ የክልሉ እግርኳስ ፌደሬሽን በደብዳቤ ጠይቋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...