By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ፈረሰኞቹ ከተከታያቸው ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሰባት ከፍ አድርገዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስወልቂጤ ከተማየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

የጨዋታ ዘገባ | ፈረሰኞቹ ከተከታያቸው ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሰባት ከፍ አድርገዋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 3 years ago
Share
SHARE

የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ22ኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ስታድየም ሲደረግ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወልቂጤ ከተማን 2 – 1 በማሸነፍ ከተከታዩ ባህርዳር ከተማ ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሰባት ከፍ አድርጓል ።

በጨዋታው በሁለቱም ክለቦች በኩል በ21ኛው ሳምንት በነበራቸው ጨዋታ ላይ በተጠቀሙት የመጀመሪያ አሰላለፍ ላይ ለውጥ ሳያደርጉበት በዚህኛው ጨዋታም ተጠቅመዋል ።

በመጀመሪያው አጋማሽ በነበረው የጨዋታ ሂደት ተመጣጣኝ ሊባል የሚችል የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ ቢታይም ወደ ግብ ቀርቦ የግብ ዕድሎች ከመፈጠር አንፃር ፈረሰኞቹ የተሻለ ጊዜን ማሳለፍ ችለው ነበር ።

- ማሰታውቂያ -

በጨዋታው በሁለቱም ቡድኖች በኩል በመሀል ላይ ብልጫ ለመውሰድ ጥረቶችን ያደረጉበትም ነበር ። በፈረሰኞቹ በኩል በተለይም በመስመሮች በኩል በሚነሱ ኳሶች የግብ ዕድሎችን ለመፍጠር ጥረቶችን አድርገዋል ።

በቅዱስ ጊዮርጊስ በኩል በነበረ የመጀመሪያ የግብ ዕድል እስማኤል ኦሮ አጎሮ ከቢንያም በላይ የደረሰውን ኳስ አስቆጠረው ተብሎ ሲጠበቅ ሳይጠቀምበት ቀርቷል ።

ከደቂቃዎች በኋላ ከቢንያም በላይ እግር የተነሳውን የማዕዘን ምት ሄኖክ አዱኛ አግኝቶ ወደ ግቦ መሞከር ቢችልም የሄኖክ ሙከራ ጠንካራ አለመሆኑን ተከትሎ ጀማል ጣሰው በቀላሉ ይዞታል ።

ወልቂጤ ከተማዎች ወደ ፊት ለመድረስ የሚያደርጓቸው ጥረቶች ውጤታማ አልነበሩም ።

በአጋማሹ የመጠናቀቂያ ደቂቃዎች ላይ ሳሙኤል አስፈሪ ከቀኝ መሰመር አሻግሮ አቤል ነጋሽ በግንባር ለመጠቀም የሞከረው ኳስ ከመከነበት አጋጣሚ ውጪ ወደ ሳጥን ለመግባት ተቸግረዋል ።

የመጀመሪያው አጋማሽም ግብ ሳይቆጠርበት ተጠናቋል ።

በሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ መቀዛቀዞች የታዩበት ነበር ።

በተጀመረ በመጀመሪያ ደቂቃ ላይም አቤል ነጋሽ በፈጣን መልሶ ማጥቃት ከጌታነህ ከበደ የደረሰውን ኳስ ሳይጠቀምበት ቀርቷል ።

በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይ በሁለቱም በኩል ወደ ፊት የመድረስ ጥረቶች ቢኖሩም ለግብ የቀረቡ የግብ ሙከራዎች ከማድረግ አንፃር ጠንካራ እንቅስቃሴ አልታየም ነበር ።

ጨዋታው 62ኛ ደቂቃ ሲደርስ ግን ኳስ እና መረብ ተገናኝተዋል ። አቤል ያለው ከቀኝ መስመር አቅጣጫ ወደ ግብ ክልል ያሻገረውን ኳስ በተቃራኒ አቅጣጫ የነበረው ረመዳን ዩሱፍ በቀጥታ ወደ በመምታት ከመረብ አሳርፏል ።

ከሁለት ደቂቃዎች በኋላም የሊጉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ አስማኤል ኦሮ አጎሮ የግብ መጠኑን 21 ያደረሰበትን ግብ አስቆጥሯል ።

በሁለት ደቂቃ ልዩነቶች ሁለት ግቦችን ያስቆጠሩት ፈረሰኞቹ በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይ ኳሱን ይዘው በመጫወት የጨዋታውን ፍሰት ለመቆጣጠር ሲጥሩ ተስተውሏል ።

በነዚህ ደቂቃዎች ላይ ጫን ብለው በመጫወት በሚነጠቁ ኳሶች በፈጣን መልሶ ማጥቃት ዕድሎች ለመፍጠር የጣሩት ወልቂጤ ከተማዎች ይህ ነው ሊባል የሚችል ጠንካራ የግብ ዕድል ሳይፈጥሩ እስከመጨረሻው ደቂቃ ድረስ ለመጓዝ ተገደዋል ።

በቅዱስ ጊዮርጊስ በኩል በ82ኛው ደቂቃ ላይ አላዛር ሳሙኤል ወደ ሳጥን ይዞ ገብቶ ለቡድን አጋሮቹ በተገቢው መልኩ ሳያደርስ የቀረው ኳስ እና ከደቂቃ በኋላ ኦሮ አጎሮ ከሳጥን ውጪ ወደ ግብ ሞክሮ የወጣበት ኳስ ምናልባትም የፈረሰኞቹን መሪነት ከፍ ማድረግ የሚችሉ አጋጣሚዎች ነበሩ ።

በ89ኛው ደቂቃ ላይም የቅዱስ ጊዮርጊስ ተከላካዮች መዘናጋትን ተከትሎ የመሀል ተከላካዩ ተስፋዬ መላኩ ወደ ሳጥን ይዞ የገባውን ኳስ ጌታነህ ከበደ አግኝቶ ከመረብ አሳርፎታል ።

በመጨረሻም ቅዱስ ጊዮርጊስ 2 – 1 በሆነ ውጤት ወልቂጤ ከተማን ረቷል ።

በ23ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው ግንቦት 3(ሐሙስ) ከ9:00 ጀምሮ ቅዱስ ጊዮርጊስ መቻልን ሲገጥም በዕለቱ ከአመሻሽ 12:00 ጀምሮ ደግሞ ወልቂጤ ከተማ ከገጣፎ ለገዳዲ ይጫወታል ።

You Might Also Like

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | በሮድዋ ደርቢ ሲዳማ ቡና አሸንፏል !!
Next Article የ2015 የኢትዮጵያ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ የዉድድር ዘመን በሲዳማ ቡና አሸናፊነት ተጠናቋል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
Uncategorized

ቡናማዎቹ ተጫዋች ለማስፈረም ተስማሙ !

hatricksport team By hatricksport team 6 years ago
የኢትዮጲያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባኤ ከሃዋሳ ወደ አዲስ አበባ ተዛወረ….
ጅማ አባጅፋር ከ ወልቂጤ ከተማ | ቀጥታ የውጤት መግለጫ
የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ከ5ኛ ሳምንት ጀሞሮ የሚቋረጡ ይሆናል
ወልዋሎ አዲግራት ዮንቨርሲቲ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌን በአሰልጣኝነት ቀጠረ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?