By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | በሮድዋ ደርቢ ሲዳማ ቡና አሸንፏል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችሀዋሳ ከተማሲዳማ ቡናየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

የጨዋታ ዘገባ | በሮድዋ ደርቢ ሲዳማ ቡና አሸንፏል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 3 years ago
Share
SHARE

የሀዋሳ ከተማ የመጀመሪያ በሆነዉ የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቀሪ  የ22ተኛ ሳምንት ጨዋታ በሮዱዋ ደርቢ ሲዳማ ቡና ሀዋሳ ከተማን 1ለ0 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

በውጤት ደረጃ ለሁለቱም ክለቦች ወሳኝ በነበረዉ የዕለቱ ጨዋታ በመጀመሪያዎቹ አምስት ያህል ደቂቃዎች ሲዳማ ቡና በጥሩ የኳስ ቁጥጥር የበላይነት እና በቀኝ በኩል ባዘነበለ የማጥቃት እንቅስቃሴ ግብ ለማስቆጠር ሲጥሩ እና ተደጋጋሚ ኳሶችን ወደ ሳጥን ሲልኩም ተስተውሏል።

በዚህም ቨ16ተኛዉ ደቂቃ ላይ ይገዙ ቦጋለ ላይ ጥፋት መሰራቱን ተከትሎ በሲዳማ የቀኝ ማጥቃት በኩል የተገኘዉን ኳስ ፍሬዉ ሰለሞን ቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ለጥቂት በግቡ አናት ላይ ወጥታለች። በ19ነኛዉ ደቂቃ ላይ ደግሞ ከተመሳሳይ ቦታ የተገኘዉን የቅጣት ምት ኳስ ፍሬዉ ወደ ሳጥን አሻምቶ ደስታ ደሙ በጭንቅላቱ ኳሷን ወደ ግብ ልኮ የነበረ ቢሆንም በተመሳሳይ ለጥቂት ወደ ዉጭ ወጥታበታለች።

- ማሰታውቂያ -

በጨዋታዉ የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ በመጠኑም ቢሆን ብልጫ የተወሰደባቸዉ እና አልፎ አልፎ በመልሶ ማጥቃቱ  አደጋ ሊፈጥሩ ሲጥሩ የነበሩት ሀይቆቹ 24ተኛዉ ደቂቃ ላይ ጥሩ ዕድል መፍጠር  ችለዉ ነበር ፤ በዚህም በጥሩ ሩጫ ከኤፍሬም አሻሞ የተሻገረለትን ኳስ ተቆጣጥሮ በሳጥኑ ጠርዝ ላይ ወደ ሲዳማ ግብ ክልል መድሀኔ ብርሀኔ የላካትን ኳስ ግብ ጠባቂው መክብብ ደገፉ በቀላሉ ተቆጣጥሯታል። በተቃራኒዉ በ29ነኛዉ ደቂቃ ላይ ሲዳማዎች ግልፅ የግብ ዕድል መፍጠር ችለዉ የነበረ ቢሆንም ይገዙ እንዲሁም ዳንኤል ዕድላቸዉን መጠቀም ሳይችሉ ቀርተዋል።

አሁንም የበላይነታቸዉን አጠናክረዉ የቀጠሉት ሲዳማዎች በ36ተኛዉ ደቂቃ ላይ ደግሞ የሲዳማ ቡናዉ የመሐል ሜዳ ሞተር ፍሬዉ ሰለሞን ጉዳት ማስተናገዱን ተከትሎ በአቤኔዘር ተተክቶ ለተጨማሪ ህክምና ወደ ሆስፒታል አምርቷል።

የመጀመሪያዉ አጋማሸ ሊገባደድ ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀሩት ደግሞ በመልሶ ማጥቃት የተገኘውን ኳስ አሊ ሱለይማን ኳሷን በፍጥነት እየገፋ በግራ በኩል ለሚገኘዉ ኤፍሬም አሻሞ አቀብሎት ተጫዋቹ በቀጥታ ስጥን ውስጥ ከገባ በኋላ ለአጥቂዉ ሙጅብ አቀብሎት የነበረ ቢሆንም ግብ ጠባቂዉ መክብብ በጥሩ ቅልጥፍና ኳሶን መልሷታል።

በተጨማሪም የመጀመሪያ አጋማሽ ተገባዶ በጭማሪ ሰዓትም አቤል እንዳለ ጥሩ ለግብ የቀረበ ሙከራን ማድረግ ቢችል ሳይሳካ ቀርቶ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ የመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ግብ በአቻ ዉጤት ተጠናቋል።

ከዕረፍት መልስ እንደመጀመሪያው አጋማሽ ሁሉ ብልጫቸዉን ያስቀጠሉት ሲዳማዎች ከአንድ ሁለት ድንቅ ለግብ የቀረቡ ሙከራዎች በኋላ በ63ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም ከሲዳማ ቡና የቀኝ ማጥቃት በኩል እንዳለ ከበደ ያሻማዉን ኳስ አጥቂዉ ፍሊፕ አጃህ በግንባሩ በመግጨት ግብ ማሰልጠኛ ማስቆጠር ችሏል።

በሲዳማ ቡና የተወሰደባቸውን ብልጫ መቋቋም ያልቻሉትን እና የኋላ የኋላ ግብ ያስተናገዱት ሀይቆቹ በመስመር አጥቂዉ አሊ ሱለይማን እና አጥቂዉ ሙጅብ ቃሲም እንዲሁም ኤፍሬም አሻሞ አማካኝነት ጥሩ ጥሩ የሚባሉ የግብ ዕድሎችን መፍጠር ችለዉ የነበረ ቢሆንም ዕቅዳቸዉ ሰምሮ ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ቀርተዋል።

ግብ ካስቆጠሩ በኋላ ጫናቸዉን አሁንም አጠናክረዉ የቀጠሉት ሲዳማዎች በግቡ ባለቤት ፍሊፕ አጃህ አማካኝነት ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ማድረግ ችለዉ የነበረ ቢሆንም ተጨማሪ ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ቀርተዉ አንድ ለዜሮ በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችለዋል። ዉጤቱን ተከትሎም ሲዳማ ቡና ነጥቡን ወደ 24 ከፍ አድርጎ አስራ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ፤ በተቃራኒው ሀዋሳ ከተማ በ31 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የ23ኛ ሳምንት ቀሪ የምድብ ጨዋታዎች በዛሬዉ እለት ሲካሄዱ በምድብ ‘ሐ’ ኮልፌ ቀራንዮ ከመመራት ተነስቶ አሸንፏል
Next Article የጨዋታ ዘገባ | ፈረሰኞቹ ከተከታያቸው ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሰባት ከፍ አድርገዋል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግድሬዳዋ ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዲሲፕሊን ውሳኔፋሲል ከነማ

ፋሲል ከነማ እና ድሬደዋ ከተማ እግር ኳስ ክለቦች ቅጣት ተላለፈባቸው።

hatricksport team By hatricksport team 4 years ago
የቀድሞ ተጫዋቾች እና አሰልጣኞች በSuper sport የቀጥታ ስርጭት በተንታኝነት….. !!
ቅዱስ ጊዮርጊስ የሙሉአለም መስፍን ውል ሲያራዝም ደስታ ደሙን አስፈርሟል
የኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ 13ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በቀጥታ /LIVESCORE/
የመቻል ስፖርት ክለብ የግብ ጠባቂ አሰልጣኞች ስልጠና ሊሰጥ ነው….
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?