መነሻ ገጽ Uncategorized 31ኛው ቶታል አፍሪካ ዋንጫ ከተጀመረ ዛሬ አራተኛ ቀኑን አስቆጥሯል።
Uncategorized

31ኛው ቶታል አፍሪካ ዋንጫ ከተጀመረ ዛሬ አራተኛ ቀኑን አስቆጥሯል።

አጋራ
አጋራ

 በጋቦን አስተናጋጅነት በመካሄድ ላይ በሚገኘው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ አራት ሁለት ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ይካሄዳሉ።

በምድብ አራት የተደለደሉት ግብፅ፣ ኡጋንዳ፣ጋና እና ማሊ የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

ዛሬ ምሽት 1 ሰዓት ላይ በሚደረግ የምድብ አራት የመጀመሪያ ጨዋታ የምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ ተካፋይ የሆነችው ኡጋንዳ ከጥቋቁር ኮከቦቹ ጋና ጋር ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል።

እንዲሁም ምሽት አራት ሰዓት ላይ የሚደረግ ጨዋታ ደግሞ የምእራብ አፍሪካዋን ማሊ ከሰሜን አፍሪካዋ ግብፅ ጋር የሚያገናኝ ይሆናል።

ትናንት ምሽት የምድብ ሶስት ጨዋታዎች የተካሄዱ ሲሆን፥ ምሽት አንድ ሰዓት ላይ የተደረገው ጨዋታ አይቮሪኮስትን ከቶጎ አገናኝቷል።

ጨዋታውም ያለ ምንም ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል። ምሽት አራት ሰዓት ላይ በተደረገ ሌላኛው የምድብ ሶስት ጨዋታ ደግሞ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን ከሞሮኮ ጋር ነበር ያገናኘው።

ጨዋታውም በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ 1ለ0 በሆነ አሸናፊነት ተጠናቋል።

በዚህም መሰረት አስተናጋጇ ጋቦን የምትገኝበት የመጀመሪያው ምድብ ጨዋታዎች በአቻ ውጤት በመጠናቀቃቸው ሁሉም 1 ነጥብ ይዘዋል።ከምድብ ሁለት ደግሞ ቱኒዝያን የረታችውሴኔጋል ምድቡን በሶስት ነጥብ እየመራች ነው።

አቻ የተለያዩት ዚምባብዌ እና አልጀሪያ ደግሞ በእኩል 1 ነጥብ ሁለተኛ እና ሶስተኛን ደረጃ ይዘዋል።

ትናንት ምሽት ጨዋታቸውን ያደረጉት ምድብ ሶስት ሀገራት ውስጥ ደግሞ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በሙሉ ሶስት ነጥብ ምድቡን በመምራት ላይ ትገኛለች። ያለ ምንም ግብ በአቻ ውጤት የተለያዩት አይቮሪኮስት እና ቶጎ በእኩል አንድ ነጥብ ከዴሞክራቲክ ኮንጎ ቀጥለው የተቀመጡ ሲሆን፥ ሞሮኮ በ0 ነጥብ ከምድቡ መጨረሻ ላይ ተቀምጣለች።

ለ23 ቀናት በሚቆየው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ላይ 16 ሀገራት በአራት ምድቦች ተደልድለው 32 ጨዋታዎችን በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

በዘንድሮውን የአፍሪካ ዋንጫ ኮትዲቯር፣ሴኔጋል፣ ጋና፣ አልጄሪያ እና ግብፅ ዋንጫውን ያነሳሉ ተብለው ቅድመ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ወስጥ ተጠቃሽ ናቸው።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
Uncategorized

ቅዱስ ጊዮርጊስ የመቶ ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገለት

ዛሬ አንጋፋውን የቅዱስ ጊዮርጊስ የስፓርት ማህበር ከገጠመው የመፍረስ አደጋ ለመታደግ የተለያዩ አካላትን...

Uncategorized

ለዋልያዎቹ መጫወትን የሚመኘው የሴሪ ኣው ክለብ ተጫዋች ማነው ?

የጣሊያን ሴሪ ኣው ክለብ ቶሪኖ ንብረት ስለሆነው አስደናቂው የአጥቂ አማካይ ተጫዋች እንንገራችሁ።...

Uncategorized

ቡናማዎቹ ተጫዋች ለማስፈረም ተስማሙ !

  በዛሬው ዕለት ግብ ጠባቂ በማስፈረም ወደ ዝውውሩ የገቡት ኢትዮጵያ ቡናማዎች ዘካሪያስ...