በ9ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፋሲል ከተማ ድል ቀንቶታል።
በአዲስ አበባ ስታዲየም አዲስ አበባ ከተማን የገጠመው ፋሲል ኤዶም ኮድዞ በ6 እና 32ኛው ደቂቃ በፍፁም ቅጣት ምት ባስቆጠራቸው ግቦች 2 ለ 0 ረቷል።መከላከያ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያደረጉት ጨዋታ ደግሞ ያለምንም ግብ ተጠናቋል።
ሊጉ ነገ ቀጥሎ ሲውል አምስት ጨዋታዎች በክልል እና በአዲስ አበባ ይደረጋሉ።የሊጉ መሪ ደደቢት ወደ አርባምንጭ ተጉዞ አርባምንጭ ከተማን የሚገጥምበት ጨዋታ መሪነቱን ለማጠናከር እንደሚያግዘው ይጠበቃል።ከደደቢት ጋር በእኩል 17 ነጥብ በግብ ተበልጦ ሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው አዳማ ከተማ በሊጉ ግርጌ ከሚገኘው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጋር 9 ስአት ላይ በአዲስ አበባ ስታድየም ይጫወታል። በተመሳሳይ 9 ስአት ላይ ጅማ አባ ቡና ከሲዳማ ቡና እንዲሁም ሀዋሳ ከተማ ከወላይታ ድቻ ጨዋታዎችን ያደርጋሉ።
ባለፈው እሁድ በኢትዮጵያ ቡና የተሸነፈው ቅዱስ ጊዮርጊስ ከድሬዳዋ ከተማ የሚያደርጉት ጨዋታ ነገ 11 ስአት ከ30 ላይ ይጀምራል።
ወልድያ ከተማ ደግሞ ኢትዮጵያ ቡናን በመጪው አርብ በመልካ ቆሌ ያስተናግዳል።
አስተያየት ይስጡ