መነሻ ገጽ Uncategorized ጅማ አባቡና ደረጄ በላይን አሰናብቶ ገብረመድህን ሀይሌን ተክቷል
Uncategorized

ጅማ አባቡና ደረጄ በላይን አሰናብቶ ገብረመድህን ሀይሌን ተክቷል

አጋራ
አጋራ

 

ጅማ አባቡና አሰልጣኝ ደረጀ በላይ ጋር ተለያይቷል።ገብረመድህን ሀይሌ ደግሞ የክለቡ አሰልጣኝ ሆነው ተሹመዋል።

ጅማ አባቡና በባለፈው አመት ከፍተኛ ሊግ የምድቡ የበላይ ሆኖ እንዲያጠናቅቅና ፕሪሚየር ሊጉን እንዲቀላቀል ያደረጉት አሰልጣኝ ደረጀ በላይ በፕሪሚየር ሊጉ ያደረጉት አጀማመር ጥሩ አለመሆኑን ተከትሎ ነው ከክለቡ ጋር የተለያዩት።

PicsArt_1485183461869

ትናንትና የባለፈው አመት የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን ቅዱስ ጊዮርጊስን በአዲስ አበባ ስታዲየም የገጠመው ጅማ አባቡና 1 ለ 1 መለያየቱ ይታወቃል።

 

አሰልጣኙ ከጨዋታው በኋላ በሰጡት መግለጫ በስራቸው ላይ ነፃነት በማጣታቸው ከክለቡ አመራሮች ጋር በመነጋገር ክለቡን ለመልቀቅ ከስምምነት ላይ ደርሻለሁ ብለዋል።

ጅማ አባቡና በፕሪሚየር ሊጉ 12 ጨዋታዎችን አድርጎ በ10 ነጥቦች ወራጅ ቀጠናው ውስጥ 14ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

አዲሱ አሰልጣኝ ገብረመድህን ሀይሌ ለቀጣዮቹ ስድስት ወራት ክለቡን በአሰልጣኝነት ይመራሉ ተብሏል።

አሰልጣኙ በፕሪሚየር ሊጉ 13ኛ ሳምንት በሜዳቸው ወልዲያ ከተማን በሚያስተናግዱበት ጨዋታ ስራቸውን በይፋ ይጀምራሉ። 

አሰልጣኝ ገብረ መድህን ሀይሌ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ከግንቦት 1 2008 እስከ መስከረም 30 2009 ድረስ ማሰልጠናቸው ይታወሳል።

ገብረ መድህን በመካከለኛውና የምስራቅ አፍሪካን ዋንጫ ኢትዮጵያ በ1980 ዓመተ ምህረት ከዚምባብዌ ጋር ለፍጻሜ ተጫውታ ዋንጫ ስታነሳ ተሰልፎ ተጫውቷል።ትራንስ ኢትዮጵያ ፤ኢትዮጵያ ቡና ፤ መድህን እና መከላከያን ደግሞ በአሰልጣኝነት መርቷል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
Uncategorized

ቅዱስ ጊዮርጊስ የመቶ ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገለት

ዛሬ አንጋፋውን የቅዱስ ጊዮርጊስ የስፓርት ማህበር ከገጠመው የመፍረስ አደጋ ለመታደግ የተለያዩ አካላትን...

Uncategorized

ለዋልያዎቹ መጫወትን የሚመኘው የሴሪ ኣው ክለብ ተጫዋች ማነው ?

የጣሊያን ሴሪ ኣው ክለብ ቶሪኖ ንብረት ስለሆነው አስደናቂው የአጥቂ አማካይ ተጫዋች እንንገራችሁ።...

Uncategorized

ቡናማዎቹ ተጫዋች ለማስፈረም ተስማሙ !

  በዛሬው ዕለት ግብ ጠባቂ በማስፈረም ወደ ዝውውሩ የገቡት ኢትዮጵያ ቡናማዎች ዘካሪያስ...