መነሻ ገጽ Uncategorized ድሬዳዋን ተቀላቅሎ የነበረው ሰለሞን ገብረመድህን ወደ ፋሲል ከተማ አመራ 
Uncategorized

ድሬዳዋን ተቀላቅሎ የነበረው ሰለሞን ገብረመድህን ወደ ፋሲል ከተማ አመራ 

አጋራ
አጋራ

image

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ላይ ለመተሐራ ስኳር ለሰበታ ከተማ ለኢትዮጵያ ቡና እና ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቡድኖች በመሀል ሜዳ ስፍራ ላይ እግር ኳስን በመጫወት ድንቅ ብቃቱን ያሳየው ሰለሞን ገብረመድህን በክረምቱ የተጨዋቾች ዝውውር መስኮት ድሬዳዋ ከተማን ተቀላቅሎ ልምምዱን መስራት ከጀመረ በኃላ አሁን ደግሞ ከክለቡ ተለያይቶ የፕሪምየር ሊጉን ውድድር ዘንድሮ ወደ ተቀላቀለው ፋሲል ከተማ አምርቷል፡፡
በመሐል ሜዳ ጥሩ ተጨዋችነቱ የሚታወቀው ሰለሞን የድሬዳዋ ከተማ እግር ኳስ ቡድንን በአሰልጣኙ ዘላለም ሽፈራው ተፈልጎ በመግባቱ መደሰቱንና ለክለቡም ውጤት ማምጣት በእዚህ ዓመት ጥሩ ብቃቱን ለማሳየት መዘጋጀቱን በቅርቡ ለወጣው ሊግ ስፖርት ጋዜጣ አስተያየቱን የሰጠ ቢሆንም ሰለሞን ምክንያቱን ባላወቀበት ሁኔታ ወደ ድሬዳዋ የገባበት ውሉ ለፌዴሬሽኑ ባለመግባቱ የቡድኑ ህጋዊ ተጨዋች ሳይሆን ቀርቷል፡፡
አሁን ግን በአሰልጣኝ ዘማሪያም ወልደጊዮርጊስ ወደሚመራው ፋሲል ከተማ በማምራት እና በመፈረም የቡድኑ ተጨዋች ሆኗል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
Uncategorized

ቅዱስ ጊዮርጊስ የመቶ ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገለት

ዛሬ አንጋፋውን የቅዱስ ጊዮርጊስ የስፓርት ማህበር ከገጠመው የመፍረስ አደጋ ለመታደግ የተለያዩ አካላትን...

Uncategorized

ለዋልያዎቹ መጫወትን የሚመኘው የሴሪ ኣው ክለብ ተጫዋች ማነው ?

የጣሊያን ሴሪ ኣው ክለብ ቶሪኖ ንብረት ስለሆነው አስደናቂው የአጥቂ አማካይ ተጫዋች እንንገራችሁ።...

Uncategorized

ቡናማዎቹ ተጫዋች ለማስፈረም ተስማሙ !

  በዛሬው ዕለት ግብ ጠባቂ በማስፈረም ወደ ዝውውሩ የገቡት ኢትዮጵያ ቡናማዎች ዘካሪያስ...