ዳሽን ቢራ ከወልዲያ ከተማ ጋር ስፖርት ክለብ ጋር የ45 ሚሊየን ብር የአጋርነት ስምምነት ተፈራረመ። የድጋፍ (ስፖንሰርሺፕ) ስምምነቱ ለሚቀጥሉት አምስት አመት የሚቆይ ነው ተብሏል።
ስምምነቱ ዛሬ ሲፈረም የቢራ ፋብሪካው 20 ሚሊየን ብሩን በቀጥታ ለክለቡ እንደሚሰጥ ተገልጿል።
ቀሪው 25 ሚሊየን ብር ደግሞ በአምስት አመት ውስጥ ከሚሸጠው ከእያንዳንዱ የዳሽን ቢራ ጠርሙስ ሁለት ሁለት ብር ተቆርጦ ለክለቡ ገቢ ይደረጋል ተብሏል።
ወልዲያ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ካለበት የገንዘብ ችግር አንፃር የተገኘው የሰፖንሰር ሺፕ ደጋፍ ክለቡን እሚጠቅም ነው፡፡
ዳሽን ቢራ ዘንድሮ ፕሪሚየር ሊጉን ለተቀላቀለው ፋሲል ከተማም ድጋፍ እንደሚያደርግ ይታወቃል።

አስተያየት ይስጡ