የመግቢያ ዋጋው ማስተካከያ ወልድያ ስፖርት ክለብ ቀጣይ በሜዳው ከኤሌክትሪክ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ጀምሮ የመግቢያ ዋጋው
ማስተካከያ ተግባራዊ ይሆናል!!
ወልድያ ስፖርት ክለብ ከመልካቆሌ ስታዲየም ወደ አዲሱ ሙሃመድ ሁሴን አል አሙዲ ስታዲየም ከተዛወረ በሁዋላ የስፖርት ቤተሰቡ በመግቢያ ዋጋው ላይ ተወደደ በሚል በርካታ ተመልካች ቅሬታውን ሲያሰማ ቆይቷል ::
የስፖርት ቤተሰቡ በተደጋጋሚ ሲያነሳው የነበረው ጥያቄ የስታዲየሙ የመግቢያ ዋጋ ከስታዲየሙ ዘመናዊነት አንጻር የመግቢያ ዋጋው ምንም ነው ነገር ግን ከህብረተሰቡ አቅም አንጻር ተወዷል የሚል የመግቢያ ዋጋው ይስተካከል ጥያቄዎች
ሲቀርቡ ተስተውሏል ይህንን የስፖርት ቤተሰቡን ጥያቄ ከግምት ውስጥ በማስገባት ቀጣይ ወልድያ ከ ኤሌክትሪክ ከሚያደርጉት
ጨዋታ ጀምሮ የስታዲየሙ የመግቢያ ዋጋ
- 70 ብር የነበረው 50 ብር
- 40 ብር የነበረው 30 ብር
- 30 ብር የነበረው ደግሞ 20 ብር ሁኗል
የነገው የወልድያና የ ሃዋሳ ጨዋታ ትኬቱ የታተመ እና ከትላንት ጀምሮ ዛሬንም ጨምሮ በርካታ ትኬቶች ከተማው ውስጥ የተሸጡ በመሆኑ የነገው የወልድያና የሃዋሳ ጨዋታ ብቻ በባለፈው ዋጋ እንደሚቀጥል ታውቋል!!
የነገው ወልድያና የሃዋሳ ጨዋታ ብቻ እንደ ባለፈው ሳምንት ተመሳሳይ የመግቢያ ዋጋው
- 70 ብር
- 40 ብር
- እና
- 30 ብር ሲሆኑ
- ከዚህ ጨዋታ በሁዋላ የሚደረጉ ጨዋታዎች
- 50 ብር
- 30 ብር
- እና
- 20 ብር እዲሆን ተደርጓል፡፡

አስተያየት ይስጡ