መነሻ ገጽ Uncategorized ​የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 6ኛ ሳምንት ጨዋታዎች እሁድ ይደረጋሉ!!!
Uncategorized

​የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 6ኛ ሳምንት ጨዋታዎች እሁድ ይደረጋሉ!!!

አጋራ
አጋራ


6ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እሁድ ቀጥሎ ስምንት ጨዋታዎችን ያስተናግዳል።   

በአዲስ አበባ ስታዲየም ሁለት ጨዋታዎች የሚደረጉ ሲሆን፥ 9 ሰዓት ላይ ደደቢት ከ ኢትዮ ኤሌክትሪክ፤ 11 ስአት ከ30 ላይ ደግሞ መከላከያ ከጅማ አባቡና ይገናኛሉ።

በክልል ስታዲየሞች ወላይታ ዲቻ ሶዶ ላይ ኢትዮጵያ ቡናን ያስተናግዳል። ኢትዮጵያ ቡና ባሳለፍነው ቅዳሜ ሲዳማ ቡናን 2 ለ 1 በማሸነፍ የመጀመሪያ ሙሉ ሶስት ነጥቡን በሊጉ ማግኘቱ ይታወሳል። በአንጻሩ ወላይታ ዲቻ በሜዳው ከድሬዳዋ ከተማ ጋር አቻ ወጥቷል።

ሁለቱ ክለቦች የሚያደርጉት ጨዋታ ደረጃቸውን ለማሻሻል ከሚደረገው ፉክክር ጎን ለጎን ከመሪ ክለቦች ላለመራቅ የሚደረግም ይሆናል።

አርባምንጭ በሜዳው ከአዲስ አበባ ከተማ ጋር የሚጫወት ሲሆን፥ ሁለቱም ክለቦች በደረጃው ሰንጠረዥ በእኩል አምስት ነጥብ 10ኛ 11ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።

ከአምስት ጨዋታ መካከልም 1 ጨዋታ ብቻ ነው ማሸነፍ የቻሉት።

በሌላ ጨዋታ የሊጉ ጠንካራ ቡድኖችን ነጥብ ያስጣለው ፋሲል ከተማ ጎንደር ላይ ሀዋሳ ከተማን ያስተናግዳል።

አዳማ ከወልዲያ፣ ሲዳማ ቡና ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ድሬዳዋ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እሁድ ከሚደረጉ ጨዋታዎች መካከል ተጠቃሽ ናቸው።

ድሬዳዋ ከንግድ ባንክ የሚያደርገው ጨዋታ 10 ሰዓት ላይ የሚጀመር ሲሆን፥ ሌሎች ጨዋታዎች 9 ሰዓት የሚደረጉ ይሆናል። ሊጉን ከአምስት ጨዋታ 10 ነጥብ መሰብሰብ የቻለው ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲመራ ሲዳማ ቡና በዘጠኝ፣ ደደቢትና አዳማ በ8ነጥብ ተከታዩን ስፍራ ይዘዋል።

ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን ጌታነህ በአምስት ሲመራ፤ ያቡን ሳላዲን እና አዳነ ግርማ በሶስት ግብ ይከተላሉ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
Uncategorized

ቅዱስ ጊዮርጊስ የመቶ ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገለት

ዛሬ አንጋፋውን የቅዱስ ጊዮርጊስ የስፓርት ማህበር ከገጠመው የመፍረስ አደጋ ለመታደግ የተለያዩ አካላትን...

Uncategorized

ለዋልያዎቹ መጫወትን የሚመኘው የሴሪ ኣው ክለብ ተጫዋች ማነው ?

የጣሊያን ሴሪ ኣው ክለብ ቶሪኖ ንብረት ስለሆነው አስደናቂው የአጥቂ አማካይ ተጫዋች እንንገራችሁ።...

Uncategorized

ቡናማዎቹ ተጫዋች ለማስፈረም ተስማሙ !

  በዛሬው ዕለት ግብ ጠባቂ በማስፈረም ወደ ዝውውሩ የገቡት ኢትዮጵያ ቡናማዎች ዘካሪያስ...