መነሻ ገጽ Uncategorized ​የቶታል አፍሪካ  ቻምፒዮንስ ሊግ እና የቶታል አፍሪካ  ኮንፌድሬሽን ዋንጫ ድልድል ዛሬ አመሻሽ ላይ ይፋ ሆኗል!!!
Uncategorized

​የቶታል አፍሪካ  ቻምፒዮንስ ሊግ እና የቶታል አፍሪካ  ኮንፌድሬሽን ዋንጫ ድልድል ዛሬ አመሻሽ ላይ ይፋ ሆኗል!!!

አጋራ
አጋራ

ቅዱስ ጊዮርጊስ እና መከላከያ የቶታል አፍሪካ  ቻምፒዮንስ ሊግና የቶታል አፍሪካ  ኮንፌድሬሽን ዋንጫ የቅድመ ማጣሪያ ፍልሚያቸውን በወጣላቸው መርሃ ግብር የሚያደርጉ ይሆናል፡፡ የፕሪምየር ሊጉ ሻምፒዮን ቅዱስ ጊዮርጊስ የሲሸልስ ሊግ ሻምፒዮኑን ኮት ደ’ኦርን ይገጥማል፡፡        

    


                                   

  የሁለቱ ክለቦች የመጀመሪያ ጨዋታ በየካቲት ወር መጀመሪያ በሲሸልስ  እና በካሜሩን የሚካሄድ ሲሆን የመልስ ጨዋታው ከሳምንት በኋላ ኢትዮጵያ ላይ የሚካሄድ ይሆናል፡፡                                   ቅዱስ ጊዮርጊስ በዚህ ዙር ኮት ዲ ኦርን አሸንፎ ካለፈ የኮንጎ ብራዛቪሉ ኤሲ ሊዮፓርድስ እና የካሜሩኑ ዩኤምኤስ ዴ ሉም አሸናፊን በ1ኛው ዙር ይገጥማል፡፡                                    በኮንፌዴሬሽን ዋንጫው የሚሳተፈው መከላከያ በቅድመ ማጣርያው የካሜሩኑ ያንግ ስፖርትስ አካዳሚን ያገኛል መከላከያ  የመጀመርያውን ጨዋታ ከየካቲት 3እስከ5 ባሉት ቀናት አዲስ አበባ ላይ ጨዋታውን ሲያደርግ ከሳምንት በኋላ የመልሱን ጨዋታ ባሜንዳ ከተማ ላይ ያደርጋል፡፡ መከላከያ ይህን ዙር ካለፈ የቱኒዚያው ሲኤስ ሴፋክሲየንን የሚገጥም ይሆናል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
Uncategorized

ቅዱስ ጊዮርጊስ የመቶ ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገለት

ዛሬ አንጋፋውን የቅዱስ ጊዮርጊስ የስፓርት ማህበር ከገጠመው የመፍረስ አደጋ ለመታደግ የተለያዩ አካላትን...

Uncategorized

ለዋልያዎቹ መጫወትን የሚመኘው የሴሪ ኣው ክለብ ተጫዋች ማነው ?

የጣሊያን ሴሪ ኣው ክለብ ቶሪኖ ንብረት ስለሆነው አስደናቂው የአጥቂ አማካይ ተጫዋች እንንገራችሁ።...

Uncategorized

ቡናማዎቹ ተጫዋች ለማስፈረም ተስማሙ !

  በዛሬው ዕለት ግብ ጠባቂ በማስፈረም ወደ ዝውውሩ የገቡት ኢትዮጵያ ቡናማዎች ዘካሪያስ...