
አዳማ ከተማ በቀጣይ ክለቡን በዋና አሰልጣኝነት የሚመሩት አሰልጣኝ ተገኔ ነጋሽ እንዲሁም ምክትላቸው አሰልጣኝ አስቻለው ሀይለ ሚካኤል መሆናቸውን አሳውቋል።
ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆነው የተመረጡት አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ እና አዳማ ከተማ እና በሳምንቱ መጨረሻ ክለቡ ከድሬዳዋ ከተማ ከሚያደርገው ጨዋታ በኋላ የሚለያዩ ሲሆን ይህን ተከትሎ ክለቡን በዋና አሰልጣኝነት የሚረከበው ማን ሊሆን ይችላል ተብሎ ሲጠበቅ ነበር።
አዳማ ከተማን በዋና አሰልጣኝነት እንዲመሩ የተመረጡት አሰልጣኝ ተገኔ ነጋሽ እንዲሁም ጤና ይስጥልኝ በምክትል አሰልጣኝነት የተመረጡት አስቻለው ሀይለሚካኤል አሰልጣኝ አሸናፊ ከክለቡ ጋር በነበራቸው ቆይታ አብረዋቸው በረዳትነት አገልግለዋል።
አስተያየት ይስጡ