መነሻ ገጽ Uncategorized በደቡብ ካስትል ሲቲ ካፕ ዋንጫ ሲዳማ ቡና ድሬዳዋ ከተማን አሸንፎ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቀለ
Uncategorized

በደቡብ ካስትል ሲቲ ካፕ ዋንጫ ሲዳማ ቡና ድሬዳዋ ከተማን አሸንፎ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቀለ

አጋራ
አጋራ

image

የደቡብ ክለቦች ወደ ፕሪምየር ሊጉ ከማምራታቸው በፊት የራሳቸውን አቋም ለመለካት እንዲችሉ ክልላቸው የሚያዘጋጅላቸው የደቡብ ካስትል ካፕ ዋንጫ ዘንድሮም በሐዋሳ አርቴፊሻል ሜዳ ላይ እየተካሄደ ሲሆን እስካሁን በሁለት ምድብ ተከፍሎ በተከናወኑ ግጥሚያዎችም ከምድብ አንድ ድሬዳዋ ከተማ ሐዋሳ ከተማን 2-1 በመርታትና ከአርባ ምንጭ ከተማ ጋር አቻ በመለያየት በ4 ነጥብ በአንደኝነት ወደ ግማሽ ፍፃሜው ሲያልፍ ሐዋሳን 1-0 የረታው አርባምንጭ ደግሞ ብዙ ባገባ ተቀድሞ በተመሳሳይ 4 ነጥብ ሁለተኛ ሆኖ አልፏል፡፡
ከምድብ ሁለት በተደረገው ጨዋታም በተጋባዥነት የቀረበው ኢትዮጵያ ቡና ሲዳማ ቡናን 4-1 ወላይታ ድቻን 2-1 እና ፋሲል ከተማን 2-1 በመርታት በ9 ነጥብ ግማሽ ፍፃሜውን ቀደም ሲል መቀላቀሉን ሲያረጋግጥ ዛሬ በተደረገው ጨዋታ ደግሞ ሲዳማ ቡና ወላይታ ድቻን 3-2 ረትቶ በ6 ነጥብ የግማሽ ፍፃሜውን የተቀላቀለ ሌላው ቡድን ሆኗል፡፡
የደቡብ ካስትል ካፕ ጥሩ ፉክክር እየተደረገበት ባለበት በአሁን ሰዓት የግማሽ ፍጻሜው ጨዋታም በድሬዳዋ ከተማ እና በሲዳማ ቡና እንደዚሁም ደግሞ በኢትዮጵያ ቡናና በአርባምንጭ ከተማ መካከል የሚከናወን ይሆናል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
Uncategorized

ቅዱስ ጊዮርጊስ የመቶ ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገለት

ዛሬ አንጋፋውን የቅዱስ ጊዮርጊስ የስፓርት ማህበር ከገጠመው የመፍረስ አደጋ ለመታደግ የተለያዩ አካላትን...

Uncategorized

ለዋልያዎቹ መጫወትን የሚመኘው የሴሪ ኣው ክለብ ተጫዋች ማነው ?

የጣሊያን ሴሪ ኣው ክለብ ቶሪኖ ንብረት ስለሆነው አስደናቂው የአጥቂ አማካይ ተጫዋች እንንገራችሁ።...

Uncategorized

ቡናማዎቹ ተጫዋች ለማስፈረም ተስማሙ !

  በዛሬው ዕለት ግብ ጠባቂ በማስፈረም ወደ ዝውውሩ የገቡት ኢትዮጵያ ቡናማዎች ዘካሪያስ...