በዚህ መሰረት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በመጀመሪያው ማጣሪያ ጨዋታ በመጪው ሐምሌ ከሜዳው ውጭ ከጅቡቲ ብሔራዊ ቡድን ጋር ይጫወታል።
የብሔራዊ ቡድኑ የመልስ ጨዋታ ደግሞ ከሳምንት በኋላ የሚደረግ ይሆናል። በደርሶ መልስ ያሸነፈው ቡድን ከቡሩንዲና ከሱዳና አሸናፊ ጋር እንደሚገናኝ ከወጣው መርሃ ግብር ለማወቅ ተችሏል። በ2018 የቻን የማጣሪያ ውድድር ታንዛኒያ ከሩዋንዳ ጋር የምትጫወት ሲሆን ቡሩንዲ ደግሞ ከሱዳን ጋር ትገጥማለች።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ለአራተኛ ጊዜ በ2016 በሩዋንዳ አስተናጋጅነት በተካሄደው ውድድር መሳተሱ የሚታወስ ነው። ዋልያዎቹ በምድብ ሁለት ከኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ፣ ከአንጎላና ካሜሩን ጋር ተደልድለው በሁለቱ ተሸንፈው በአንዱ ደግሞ አቻ ወጥተው በአንድ ነጥብ ብቻ በጊዜ ተሰናብተዋል።
ለ5ኛ ጊዜ በ2018 በሚካሄደው የቻን ውድድር 16 አገራት የሚሳተፉ ሲሆን ውድድሩ በኬንያ አስተናጋጅነት በሚቀጥለው ዓመት ጥር ላይ የሚደረግ ይሆናል። የቻን ውድድር እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2009 ከተጀመረ ወዲህ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ሁለት ጊዜ፣ ቱኒዚያና ሊቢያ ደግሞ አንድ አንድ ጊዜ ዋንጫውን አንስተዋል።
አስተያየት ይስጡ