መነሻ ገጽ U-20 ብሄራዊ ቡድን በብዙ ደጋፊዎች የታጀበው የኢትዮጵያ እና የብሩንዲ ከ20 አመት በታች የሴቶች ብሄራዊ ቡድን ጨዋታ በኢትዮጵያ አሸናፊነት ተጠናቀቀ
U-20 ብሄራዊ ቡድንሉሲዎቹ

በብዙ ደጋፊዎች የታጀበው የኢትዮጵያ እና የብሩንዲ ከ20 አመት በታች የሴቶች ብሄራዊ ቡድን ጨዋታ በኢትዮጵያ አሸናፊነት ተጠናቀቀ

አጋራ
አጋራ

 

ከሜዳ ውጭ 5 ለ 0 አሸንፎ ሰፊ እድል ይዞ የመጣው ብሄራዊ ቡድናችን 2 ለ 1 በሆነ ጠባብ ውጤት አሸንፏል።

ለተመልካች ማራኪ የነበረው የመጀመሪያው አጋማሽ የኢትዮፕያ ብሄራዊ ቡድን ሙሉ ለሙሉ ብልጫ ወስዶ ተጫውቷል ሁለት ጎልም ማስቆጠር ችለዋል ተስፋ ሰጭ እንቅስቃሴ ባሳዩበት ጨዋታ ብዙ ጎል የሚሆኑ ኳሶችን አባክነዋል ።በ27ኛው ደቂቃ ስራ ይግዛው በቀኝ መስመር ከፔናሊቲ ቦክስ ውጭ አስደናቂ ጎል አስቆጥራለች። ተጨማሪ ጎል ለማግባት ጫና ፈጥረው የተጫወተው ብሄራዊ ቡድናችን በ30ኛው ደቂቃ አልጋነሽ ካልሳ ቅጣት ምት አስቆጥራ ልዩነቱን ሁለት አድርጋለች።

በሁለተኛው አጋማሽ ብዙም ሳቢ ያልነበረው ጨዋታው በቡሩንዲ በኩል የታክቲክ ለውጥ በማድረግ ተጫዋቾችን መሀል ሜዳ ላይ ተደርድረው ኦፍ ሳይድ በማስገባት የጨዋታውን እንቅስቃሴ ለመገደብ ሞክረው ተሳክቶላቸዋል በ55 ደቂቃ ላይ ያገኙትን ቅጣት ምት ወደ ጎል ቀይረው ውጤቱን 2-1 ማድረግ ችለዋል ጨዋታውም በዛው ውጤት ተጠናቋል ።

 

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ሉሲዎቹኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

ኢትዮጵያዊቷ ኮከብ በታንዛኒያ የመጀመሪያ ዋንጫዋን አሳካች

የሉሲዎቹ ወሳኝ ተጫዋች የሆነችው አረጋሽ ካልሳ ከክለቧ ያንጋ ፕሪንሰስ ጋር የመጀመሪያ ዋንጫዋን...

ሉሲዎቹዜናዎች

“አሸንፈን እንደምናልፍ በጣም እርግጠኞች ነን” ሎዛ አበራ “ተጋጣሚያችን ከኛ የተሻለ ምንም ነገር የለውም” አሰልጣኝ ዮሴፍ ገብረወልድ

የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የ2026 የአፍሪካ ዋንጫ አንደኛ ዙር የማጣሪያ የመልስ ጨዋታውን...

ሉሲዎቹዜናዎች

አሰልጣኝ ዮሴፍ ገብረወልድ ለ29 ተጫዋቾች ጥሪ አደረጉ

የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዮሴፍ ገብረወልድ ከኡጋንዳ ብሔራዊ ቡድን ለሚጠብቃቸው የአፍሪካ...