የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዮሴፍ ገብረወልድ ከኡጋንዳ ብሔራዊ ቡድን ለሚጠብቃቸው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ለ29 ተጫዋቾች ጥሪ አድርገዋል።
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዘጠኝ ተጫዋቾችን በማስመረጥ ቀዳሚ ቡድን ሲሆን ሀዋሳ ከተማ ስድስት ተጫዋቾችን አስመርጧል።
በግብ ጠባቂ ታሪኳ በርገና ፣ ቤተልሔም ዮሐንስ እና ሮማን አምባዬ ተመርጠዋል።
በተከላካይ አሳቤ ሙሶ ፣ ታሪኳ ዴቢሶ ፣ ትዕግስት አዳነ ፣ ፀሐይነሽ ጁላ ፣ ዕፀገነተ ብዙነህ ፣ ብርቄ አማረ ፣ ማህደር ባየህ እና ፀጋ ንጉሴ ተካተዋል።
- ማሰታውቂያ -
በአማካይ ቦታ እመቤት አዲሱ ፣ ሰናይት ቦጋለ ፣ ፅዮን ፈየራ ፣ ማዕድን ሳህሉ ፣ ቤተልሔም መንተሎ ፣ ዕፀገነት ግርማ ፣ መሳይ ተመስገን ፣ ብርቱካን ገብረክርስቶስ ፣ ዙፋን ደፈርሻ እና ስመኝ ምህረት ተመርጠዋል።
ሶስት ተጫዋቶችን ከውጪ ሀገራት ሊጎች ባካተተው የአጥቂ ቦታ ላይ ሎዛ አበራ ፣ አርየት ኦዶንግ ፣ አረጋሽ ካልሳ ፣ ሴናፍ ዋቁማ ፣ እሙሽ ዳንኤል ፣ ምርቃት ፈለቀ ፣ ንግስት በቀለ እና ማህሌት ምትኩ ጥሪ ተደርጎላቸዋል።
ብሔራዊ ቡድኑ ከኡጋንዳ ጨዋታ ቀደም ብሎ አስቀድሞ ከጁቡቲ አቻው ጋር ሁለት የአቋም መለኪያ ጨዋታዎችን በአዲስ አበባ የካቲት 5 እና የካቲት 9 ያደርጋል።
ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ነገ ጥር 25 ከ8:00 ጀምሮ ጋራ ላይ ሆቴል በመገኘት ሪፖርት በማድረግ እንዲሰባሰቡ ጥሪ ቀርቦላቸዋል።


