By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ታላቁ ደርቢ ያለ ግብ ሲጠናቀቅ አሊቶዎቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ ድል ቀንቷቸዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስሲዳማ ቡናስሁል ሽረየጨዋታ ዘገባ

ታላቁ ደርቢ ያለ ግብ ሲጠናቀቅ አሊቶዎቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ ድል ቀንቷቸዋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 1 year ago
Share
SHARE

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት መደረግ ሲጀምሩ የሸገር ደርቢ ያለ ግብ ሲጠናቀቅ ሲዳማ ቡና ስሁል ሽረን አሸንፏል።

በዕለቱ ቀዳሚ መርሐግብር ተጠባቂ በነበረው እና ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ቴዎድሮስ ምትኩ በርካታ አወዛጋቢ ውሳኔዎችን ባሳለፉበት የሸገር ደርቢ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል።

የሀገሪቱ ትልቁ ደርቢ በሆነው በዚህ መርሐግብር ምንም እንኳን እንደ ቀደሙት አመታት ባይሆንም በዘንድሮው የውድድር ዘመን ከተደረጉት ጨዋታዎች አንፃር በርካታ ቁጥር ያላቸው ደጋፊዎች ተገኝተዋል።

የጨዋታው የመጀመሪያው አጋማሽ እምብዛም በሙከራዎች ያልታጀበ ሲሆን በሁለቱም በኩል በተለይም በመስመር በኩል የሚደረጉ የማጥቃት ሂደቶች ውጤታማ አልነበሩም።

- ማሰታውቂያ -

ወደ ግብ ክልል በመድረስ የተሻሉ የነበሩት ቅዱስ ጊዮርጊሶች በፍፁም ጥላሁን በኢትዮጵያ ቡና በኩል ደግሞ በበፍቃዱ አለማየሁ ያደረጓቸው ሙከራዎች በግብ ጠባቂዎቹ ተመልሰዋል።

በአጋማሹ ተገኑ ተሾመ በሳጥኑ የቀኝ አቅጣጫ ይዞት የገባውን ኳስ ይዞ ለማለፍ ሲሞክር በበፍቃዱ አለማየሁ ጥፋት ቢሰራበትም የጨዋታው ዋና ዳኛ ቴዎድሮስ ምትኩ በዝምታ ማለፋቸው አነጋጋሪ ሆኗል።

በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ላይ ከነበሩት ክስተቶች መካከል የበረከት ወልዴ መጎዳት ሲሆን ተጫዋቹ ለተጨማሪ ህክምና ወድያውኑ ወደ ሆስፒታል ተወስዷል።

የሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ የተሻለ ፉክክር ፣ የተሻሉ የግብ ሙከራዎች እንዲሁም በርካታ ካርዶችም የተመዘዙበት ነበር።

በጨዋታ ረገድ ቡናማዎቹ በአማካይ ክፍል ላይ አሜሪካዊውን ኪሩቤል ደሳለኝ እና ሚኪያስ ፀጋዬን ቀይረው በማስገባት ያደረጉት የተጫዋቾች ለውጥ በተለይም በመሀል ሜዳው ላይ ብልጫ እንዲወስዱ ያስቻላቸው ሲሆን ጠንካራ የግብ ሙከራዎችንም ማድረግ ችለው ነበር።

በአጋማሹ ዲቫይን ዋቹኩዋ ፣ ኪሩቤል ደሳለኝ ፣ አንተነህ ተፈራ እንዲሁም ሚኪያስ ፀጋዬ ለግብ የቀረቡ ጠንካራ የግብ ዕድሎችን መፍጠር ችለው ነበር።

በተለይም ሚኪያስ ፀጋዬ የግቡ ቋሚ የመለሰበት እንዲሁም አንተነህ ተፈራ ለጥቂት ከግቡ አግዳሚ በላይ የወጣበት የግንባር ኳስ ለቡናማዎቹ አስቆጪ የግብ ሙከራዎች ነበሩ።

በቅዱስ ጊዮርጊስ በኩል ደግሞ ፍፁም ጥላሁን እና አብዱ ሳሚዮ ቻታኮራ ከቅጣት ምት በቀጥታ ወደ ግብ ያደረጓቸው ጠንካራ ሙከራዎች በዳንላድ ኢብራሂም በግሩም ሁኔታ ግብ ከመሆን ድነዋል።

በሁለተኛው አጋማሽ በፍፁም ጥላሁን እና በቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና ተጫዋች አብዱልሀፊዝ ቶፊቅ ላይ በፍፁም ቅጣት ምት ሳጥኖች ውስጥ ጥፋት ቢሰራባቸውም በጨዋታው አወዛጋቢ ውሳኔዎችን ሲወስኑ በነበሩት ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ቴዎድሮስ ምትኩ በዝምታ ታልፈዋል።

ጨዋታው ያለ ግብ ከተጠናቀቀ በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥቡን 29 ያደረሰ ሲሆን ኢትዮጵያ ቡና በበኩሉ ነጥቡን 23 አድርሷል።

በ19ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሀድያ ሆሳዕና እንዲሁም ኢትዮጵያ ቡና ከመቻል በመጪው ቅዳሜ የካቲት 1 ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ደግሞ ሲዳማ ቡና ስሁል ሽረን 1 – 0 በማሸነፍ ከአራት ተከታታይ ጨዋታዎች በኋላ ወደ ድል ተመልሷል።

አመሻሽ 12:00 ጀምሮ በተደረገው የሲዳማ ቡና እና ስሁል ሽረ ጨዋታ ደግሞ የመስፍን ታፈሰ የ50ኛ ደቂቃ ግብ ለአሊቶዎቹ ሶስት ነጥቦችን ለማሳካት በቂ ነበር።

ውጤቱንም ተከትሎ ሲዳማ ቡና ነጥቡን 22 በማድረስ በጊዜያዊነት ከ12ኛ ወደ 9ኛ ደረጃ ከፍ ማለት ችሏል።

ስሁል ሽረ በበኩሉ የውድድር ዓመቱን ስምንተኛ ሽንፈት በማስተናገድ በወራጅ ቀጠና ውስጥ ለመቆየት ተገዷል።

በቀጣይ ሳምንት መርሐግብር ሲዳማ ቡና ከአዳማ ከተማ እንዲሁም ስሁል ሽረ ከወልዋሎ አዲግራት ይጫወታሉ።

You Might Also Like

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article አሰልጣኝ ዮሴፍ ገብረወልድ ለ29 ተጫዋቾች ጥሪ አደረጉ
Next Article ቅዱስ ጊዮርጊስ የዳኝነት በደል ደርሶብኛል በማለት ቅሬታውን አቀረበ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎችዋልያዎቹየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ ሁለት የወዳጅነት ጨዋታዎችን እንደሚያርጉ ታዉቋል !!

Ermias Misganaw By Ermias Misganaw 5 years ago
ኢትዮጵያ ከ ዩጋንዳ | ቀጥታ የውጤት መግለጫ
ወልዋሎ ሄኖክ ገምቴሳን አስፈርሟል
ETHIOPIAN PREMIER LEAGUE DEBUTS TODAY
ኢትዮጵያ ቡና ተመስገን ዳናን በይፋ አሰናበተ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?