የሉሲዎቹ ወሳኝ ተጫዋች የሆነችው አረጋሽ ካልሳ ከክለቧ ያንጋ ፕሪንሰስ ጋር የመጀመሪያ ዋንጫዋን አሳክታለች።
አረጋሽ ያሳካችው ዋንጫ የሴቶች ቀንን በማስመልከት በታንዛኒያ በአራት ታላላቅ የሴት ክለቦች መካከል “ሳምያ ሱፐር ካፕ” በሚል ስያሜ ለመጀመሪያ ጊዜ በተደረገ ውድድር ነው።
ትናንት በተደረገው የፍፃሜ ጨዋታም አረጋሽ ካልሳን የያዘው ያንጋ ፕሪንሰስ ጄኪቲ ኩዊንስን 3 ለ 0 በማሸነፍ የዋንጫው ባለቤት ሆኗል።
በጨዋታውም አረጋሽ የመጀመሪያውን ግብ ያስቆጠረች ሲሆን በግማሽ ፍፃሜውም ፋውንቴን ጌትስ ፕሪንሰስን 7 ለ 0 ሲያሸንፉ አንድ ግብ አስቆጥራ ነበር።
- ማሰታውቂያ -



