መነሻ ገጽ መቐለ ከተማ በሽቶ ሚድያ ፕሮዳክሽንና ትግራይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ኣዘጋጅነት ለመጀመርያ ጊዜ ሚካሄደው ትግራይ ዋንጫ ከመስከረም 26-ጥቅምት 4 በግዙፋ ትግራይ ስታድየም እንደሚካሄድ ዛሬ በተካሄደው ዕጣ ማውጣት ስነ-ስርዓት ተገልፅዋል።
መቐለ ከተማሽረ እንዳስላሴትግራይ ዋንጫአክሱም ከተማወልዋሎየትግራይ እግር ኳስ ፌዴሬሽንደደቢት

በሽቶ ሚድያ ፕሮዳክሽንና ትግራይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ኣዘጋጅነት ለመጀመርያ ጊዜ ሚካሄደው ትግራይ ዋንጫ ከመስከረም 26-ጥቅምት 4 በግዙፋ ትግራይ ስታድየም እንደሚካሄድ ዛሬ በተካሄደው ዕጣ ማውጣት ስነ-ስርዓት ተገልፅዋል።

አጋራ
አጋራ

ስድስት ክለቦች በሁለት ምድብ ተከፍለው በሚወዳደሩበት ትግራይ ዋንጫ የክልሉ ክለቦች የሆኑት መቐለ ከተማ፣ወልዋሎ ዓ/ዩኒቨርሲቲ፣ሽረ እንዳስላሴ፣ደደቢት፣ ኣክሱም ከተማ እንዲሁም ድሬዳዋ ከተማን በተጋባዥነት ያስተናግዳል።

ትላንት 9 ሰዓት በትግራይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፅሕፈት ቤት የተሳታፊ ክለቦች ተወካዮችና የውድድሩ ኣዘጋጆች በተገኙበት በተካሄደው ዕጣ ማውጣት ስነስርዓት ላይ እንደተገለጸው ከስታድየም መግቢያ ከሚገኘው ገቢ 70% ለተሳታፊ ክለቦች(ከተጋባዡ ድሬዳዋ ውጪ) በተጫወቱት ጨዋታ መጠን እንደሚከፋፈል፣20% ለሽቶ ሚዲያ ፕሮዳክሽን፣10% ለትግራይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እንደሚሆን፤ በውድድሩ በተጋባዥነት ሚሳተፈው ድሬዳዋ ከተማ ከስታድየም መግቢያ ከሚገኘው ገቢ እንደማይካፈል ሆኖም የውድድሩ ኣሸናፊ ሚሆን ከሆነ ለውድድሩ ሚዘጋጀው ዋንጫ እና ሽልማት እንደሚወስድ ተገልጽዋል።

የውድድሩ ፎርማት በተመለከተ ከውድድሩ ኣዘጋጆች በሁለት ምድብ ተከፍለው እንዲጫወቱ የሚል ሃሳብ ሲያቀርቡ ደደቢት፣መቐለ፣ወልዋሎ እና ሓወልቲ ኣክሱም በፎርማቱ ሲስማሙ ሽረ እንዳስላሴ እና ድሬዳዋ ከተማ ስድስቱ ክለቦች በዙር ኣንድ ክለብ 5 ጨዋታዎችን እንዲያደርግ የሚል ሃሳብ ኣቅርበዋል፤ፎርማቱን ለመወሰን በተሰጠው ድምጽ በሁለት ምድብ ተከፍሎ ይካሄድ ሚለው ከስድስት ድምጽ ኣራቱን በማግኘቱ በምድብ ተከፍሎ እንዲካሄድ ተወስኗል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ወልዋሎዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የወልዋሎ ተጫዋቾች ልምምድ አቁመዋል

በአሰልጣኝ ግርማ ታደሠ የሚመሩት ወልዋሎዎች ልምምድ መስራትን አቁመዋል። በተጫዋቾች የደመወዝ አለመክፈል ጉዳይ...

ወልዋሎዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ወልዋሎ ናይጄሪያዊ አጥቂ አስፈረመ

ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ አራተኛውን የአጋማሹን አዲስ ፈራሚ በእጃቸው አስገብተዋል። በአሰልጣኝ ግርማ ታደሠ...

ወልዋሎዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ

ከፈረሰኞቹ ጋር የተለያየው አፈወርቅ ሐይሉ የቀድሞው ክለቡን ተቀላቀለ። በአማካይ ስፍራ ላይ ከተጠናቀቀው...