መነሻ ገጽ Uncategorized ​በሊጉ ኢትዮጵያ ቡና ድል ሲቀናውመከላከያ  አቻ ተለያይቷል
Uncategorized

​በሊጉ ኢትዮጵያ ቡና ድል ሲቀናውመከላከያ  አቻ ተለያይቷል

አጋራ
አጋራ

በ13ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ድል ሲቀናው ፋሲል ከተማ ነጥብ ተጋርቶ ወጥቷል።

ኢትዮጵያ ቡና ሳሙኤል ሳኑሚ በ69ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ብቸኛ ግብ ያሸነፈው። በዚህም ፋሲል ከተማን በአንድ ነጥብ በልጦ በ20 ነጥብ 5ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በበኩሉ ከወላይታ ድቻ ጋር ተጫውቶ ነጥብ ተጋርቶ ወጥቷል።

አላዛር ፋሲካ በ1ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ ወላይታ ድቻ መምራት ቢጀምርም ከአምስት ደቂቃ በኋላ ፍቅረስላሴ ተክለብርሃን ንግድ ባንክን አቻ አድርጓል።

በ43ኛው ደቂቃ ደግሞ ቢንያም በላይ ንግድ ባንክን ወደ መሪነት መልሷል፤ ከዚያም በ83ኛው ደቂቃ በዛብህ መለዩ ለወላይታ ድቻ የአቻነቷን ግብ አስቆጥሯል።

ባለፈው ሳምንት በሊጉ ሁለተኛውን ሽንፈቱን በደደቢት ያስተናገደው ፋሲል ከተማ ከመከላከያ ጋር ያደረገው ጨዋታ 2 ለ 2 በሆነ ውጤት ተጠናቋል።

ለፋሲል አብዱራህማን ሙባረክ ሁለቱንም ግቦች አስቆጥሯል። ማራኪ ወርቁ እና ሳሙኤል ታዬ ደግሞ መከላከያን አቻ ያደረጉ ጎሎች አስቆጥረዋል።

በጨዋታው የመከላከያው ምንይሉ ወንድሙ በ50ኛው ደቂቃ በሁለት ቢጫ ካርድ ከሜዳ ተወግዷል።

ፕሪሚየር ሊጉ ዛሬም ሲቀጥል በክልል ከተሞች ሶስት፤ በአዲስ አበባ ደግሞ ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። በክልል ከተሞች ጅማ ላይ ጅማ አባቡና ወልድያ ከተማን ሲገጥም፣ አርባምንጭ ከተማ ሲዳማ ቡናን እንዲሁም ሀዋሳ ከተማ ድሬዳዋ ከተማን በተመሳሳይ 9 ስአት ላይ ያስተናግዳሉ። 22 ነጥብ በመሰብሰብ 3ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ 9 ስአት ላይ ኢትዮ ኤሌክትሪክን ይገጥማል።

ዛሬ የሊጉ መሪዎች አዳማ ከተማ እና ደደቢት 11 ስአት ከ30 ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታም ተጠባቂ ነው።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
Uncategorized

ቅዱስ ጊዮርጊስ የመቶ ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገለት

ዛሬ አንጋፋውን የቅዱስ ጊዮርጊስ የስፓርት ማህበር ከገጠመው የመፍረስ አደጋ ለመታደግ የተለያዩ አካላትን...

Uncategorized

ለዋልያዎቹ መጫወትን የሚመኘው የሴሪ ኣው ክለብ ተጫዋች ማነው ?

የጣሊያን ሴሪ ኣው ክለብ ቶሪኖ ንብረት ስለሆነው አስደናቂው የአጥቂ አማካይ ተጫዋች እንንገራችሁ።...

Uncategorized

ቡናማዎቹ ተጫዋች ለማስፈረም ተስማሙ !

  በዛሬው ዕለት ግብ ጠባቂ በማስፈረም ወደ ዝውውሩ የገቡት ኢትዮጵያ ቡናማዎች ዘካሪያስ...