By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: “ሳላሀዲን ብቻ ሣይሆን እኛም እንደተመታን ነው የቆጠርነው…”ምንተስኖት አዳነ/የቅዱስ ጊየርጊስ አምበል/ ክፍል 2
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ቅዱስ ጊዮርጊስThe BiG Interview

“ሳላሀዲን ብቻ ሣይሆን እኛም እንደተመታን ነው የቆጠርነው…”ምንተስኖት አዳነ/የቅዱስ ጊየርጊስ አምበል/ ክፍል 2

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 6 years ago
Share
SHARE

“ሳላሀዲን ብቻ ሣይሆን እኛም እንደተመታን ነው የቆጠርነው…”

“የኮሮና ቫይረስን መመለስ የሚቻለው በፀሎት ብቻ ይመስለኛል”

“በገዛ ሜዳህ በደጋፊህ… ክልል ስትሄድ ደግሞ በተጋጣሚ ደጋፊ ጫና ውስጥ ሆነህ ውጤት መጠበቅ ይቻላል?”

ምንተስኖት አዳነ/የቅዱስ ጊየርጊስ አምበል/

- ማሰታውቂያ -

ምንተስኖት፡- /ሳቅ በሳቅ../ አልቀበልም ይሄ ቀልድ ይመስለኛል፡፡ ፋብሪጋዝኮ የአርሰናልን፣ የቼልሲና የባርሴሎናንን ማሊያኮ ስሟል፡፡ እንደውም ተጨዋቹ የሚስመው ብሩን ነው ብዬ አምናለሁ …ማሊያ ሳመና
ክለቡን ይወዳል ብዬ አልቀበልም/ሳቅ/

ሀትሪክ፡- መጠጥ፣ ጫት… ሌሎች ሱሶች.. ለእግር ኳስ ተጨዋች አስጊ አይደለም?
ምንተስኖት፡- ምንም ጥያቄ የለውም.. እግር ኳስ ከሚከለክለው መታቀብ አለብን፡፡ በግሌ ካላስፈላጊና አጓጉል ከሆኑ ነገሮች ንፁህ ነኝ ተጨዋች ስለሆንኩ ሳይሆን በቃ ስለማልፈልግና ስለማይጠቅምም ነው
በእምነትም ይሁን ከጤና አንፃር ስታየው አያስኬድም… የተጨዋችነት ዘመን ቢበዛና ከበርታህ ከ20 አመት አይበልጥም በእነኚህ አመታት ደግሞ ብዙ ነገሮች ሊፈጠሩ ይችላሉና ያሰብካቸውን አመታትን ለመጫወት ካሰብክ
ራስን መጠበቅ የግድ ነው… በተለይ ከሱስ መቆጠብ በደንብ እረፍት ማድረግን ይጠይቃል ባይ ነኝ፡፡

ሀትሪክ፡-በቅዱስ ጊዮርጊስ ማሊያ የጨዋታ ዘመንህ የመጨረስ ህልም አለህ?

ምንተስኖት፡- የምመኘው እንደዚያ ነው…. የሌላ ክለብ ማሊያ ባልለብስ ደስ ይለኛል፡፡ በጊዮርጊስ ማሊያ የጨዋታ ዘመኔን ባቆም እመርጣለሁ፡፡ ዘንድርኮ 12ኛ አመቴን ይዣለሁ… ሲ ቡድን ላይ 2 አመት ዋናው
ቡድን ላይ ደግሞ 10 አመቴን ይዣለሁ… ከዚህም በኋላ በእግር ኳሱ ውስጥ ብዙ የመቆየት አላማ የለኝም፡፡ አቅሜን ስመለከተው ብዙ አመት እንደውም እስከ 10 አመት ድረስ ልጫወት እችላለሁ እዚያ መድረስ ግን
አልፈልግም ቶሎ ማቆምን እመርጣለሁ፡፡

ሀትሪክ፡-ምንቴ ብዙ የመረረህ ነገር ያለ ይመስላል ?

ምንተስኖት፡- /ሳቅ/ ብዙ ደስ የማይሉ ነገሮች ኳሱ ውስጥ ታገኛለህ.. ደስ የሚሉ ነገሮች መኖራቸው ሳይረሳ….የትኛውም ሙያ ላይ ቻሌንጆች አሉ… እግር ኳስ ላይ መኖር ከምፈልገው ህይወት አንፃር ብዙ
የማይስማሙ ነገሮች አሉት በግሌ ብዙ ነገሮች አይመቹኝምና ቶሎ ብወጣ ደስ ይለኛል፡፡ በጊዮርጊስ ማሊያ ዘመኔን ቶሎ ብጨርስ ደስ ይለኛል፡፡

ሀትሪክ፡-እንደ አምበልነትህ የተጋጣሚ ቡድን ደረጃና የሌሎች ጨዋታ ውጤት የመከ ታተሉ ነገር ላይ ጎበዝ ነህ አሉኝ… አምበል ስለሆንክ ይሆን?

ምንተስኖት፡- አምበል ስለሆንኩ ብቻ ሣይሆን መረጃ የማየት ልምድ አለኝ፡፡ በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ደግሞ መረጃዎች ይወጣሉ.. ይህን እከታተላለሁ፡፡ በተለይ በድረ ገጾች ላይ ሙሉ መረጃ ሲለቀቅ አያለሁ፡፡
ኃላፊነቴ ደግሞ ያስገድደኛል ብዙ መረጃዎችን አይቼ ስለተጋጣሚ ያለውን እውነት በመሰብሰብ ለቡድኑ አሰልጣኞች መረጃ የመስጠት ባህል አለኝ፡፡ በነገራችን ላይ ይሄ መረጃ ተከታትሎ ሙሉ ሆኖ መገኘት የቆየ ባህሪዬ ነው፡፡

ሀትሪክ፡- በአን ድ ቦታ ላይ ብቻ አለመጫወትህ እድገትህ ላይ ተፅዕኖ አልፈጠ ረብህም?

ምንተስኖት፡- ከበረኛ በስተቀር ሁሉም የሜዳ ክፍል ላይ ተጫውቻለሁ የመጀመሪያ ጨዋታ በጊዮርጊስ ማሊያ ያደረ ኩት በሚቾ ጊዜ ነው… ታች እያለውም የተከላካይ አማካይ ነበርኩ የምወደው ቦታም ያንን ነው ወደ
ዋናው ቡድን ሳድግም ረጅም ጊዜ የተጫወትኩት በዚህ ቦታ ላይ ነበር አሰልጣኞች ሲቀያየሩ የ የራሣቸው ሃሣብ አላቸው…. ያንን ማክበር ነበረብኝ አክብሬያለሁ፡፡ የማልረሳውም በአንድ ጨዋታ ላይ የገጠመኝ ነገር ነው…
በዚህ ጨዋታ ላይ ተከላካይ ሆኜ ገባሁ ከዚያ ግብ እንቢ ሲል አማካይ ሆንኩ.. ረጅም ሰዓት ግብ ሲጠፋ አጥቂ ሆንኩና እድለኛ ሆኜ ግብ አገባሁ… የሚገርመው ተመልሰህ ተከላክል ተብዬ ተከላካይ ሆኛለሁ፡፡ ይህን
አልረሳውም በእርግጥ አንድ ቦታ ላይ አለመጫወቴማ ተፅዕኖ አለው… ብዙም ነገር አጥቼበታለሁ ግን ደግሞ ክለቤ የሚለኝን ማድረጌ የግድ በመሆኑ አልተከፋሁም፡፡

ሀትሪክ፡-ከአባይ ግድብ ጋር ተያይዞ የግብጾችን ድንፋታ እንዴት አየኸው?

ምንተስኖት፡- አዎ ሰሞኑን ውዝግብ ነበርና በተለያየ ሚዲያ ስከታተል እንደነበረው ግድቡ ልዩነትን ፈጥሯል፡፡ ሠላም አውርደው ሀገራችንን በሚጠቅም መንገድ ላይ ተስማምተው ግድቡ ተገድቦ እናያለን ብዬ አስባለው፡፡
ጦርነት ባይኖር ደስ ይለኛል ቢሰማሙ እመርጣለሁ፡፡

ሀትሪክ፡- የእግር ኳስ በቀልስ አያስፈልገ ንም ትላለህ?

ምንተስኖት፡- /ሳቅ በሳቅ/ አሁን ላይ ምንም መናገር አይቻልም ግልፅ ያለ ነገርም የለም፡፡ በኳሱ በርግጥ ግብፅም የበላይ ናት ይህን ማመን አለብን፡፡ ከተሰራ ግን ለውጥ እንዲመጣ አምናለው፡፡ ታላላቅ የአለማችን
ሊጎች ላይ በመጫወት ይበልጡናል፡፡ በርግጥ ኳሱ ከአባይ ግድብ ጋር በተያያዘ ምንም የሚያገናኘው ነገር የለም፡፡ ያም ቢሆን ግብፅን ማሸነፍ ደስ ይላል እንደተጨዋች የተሻለ ነገር ሰርተን እንደምንለወጥ ተስፋ አደርጋሁ፡፡
በሊግ ደረጃ የግብፅ ሊግ ከኛ ይሻላል ከሰራንና ከበረታን በሊግም ሆነ በብሔራዊ ቡድን ደረጃ የማንበልጥበት ምክንያት ግን የለም፡፡ ሰርተውና ኳስ ላይ ትኩረት አድርገው ካደጉ እኛም መለወጥ እንችላለን ብዬ አምናለሁ፡፡
ዛማሊክእና ኢ.ኤን.ፒ.ፒ አይን ጨምሮ ብዙ የግብፅ ክለቦችን በሻምፒዮንስ ሊግና በኮንፌዴሬሽን ካፕ ገጥሜ አይቻቸዋለው… ከትልቁ ክለብ ዛማሊክ ጋር በደርሶ መልስ ተጫውተን የተሸነፍነው እድለኛ ስላልነበርን ነውና
ከበረታን ማደግ እንችላለን እነርሱ እየሰሩ እያደጉ እየተለወጡ ሲመጡ እኛ ሀገር ግን በአንድ አጋጣሚ አንድ ውጤት ይመጣና ይቆማል አንቀጥምልበትም… በተቻለ መጠን ጠንክረን ከሰራን ግን የተሻልን መሆን እንችላለን፡፡

ሀትሪክ፡-ለኢትዮጵያ ምን ትመኛ ለህ?

ምንተስኖት፡- ደጋግሜ ተናግሬ የለሁ… ለኢትዮጵያ እንዲህ አይነት ነገር እመኛለሁ ማለት አልፈልግም ሚዲያ ላይ ቀርቤ የማቀርበው ምኞትም ምንም አይጠቅምም… የሚጠቅመው ለፈጣሪ መማፀን መፀለይ
ሀገራችን ሠላም እንድትሆን አምላክን መለመን ነው የሚያዋጣው… ብዙዎች ብዙ ብለዋልኮ… ግን መፍትሔ አልመጣም ለችግሩ መፍትሔ ከራስ አለመጀመር ይመስለኛል፡፡ የግል ሠላም የሌለው ሰው ለኢትዮጵያ ሠላም
ማሰብ አለበት ብዬ አላስብም፡፡ መጀመሪያ ቅን መሆን ከቻልን ራስ ወዳድነታችን ካስቀረን ከዚያ በኋላ ፈጣሪን ብንለምንኮ ይሰማናል፡፡ ዋናው ሁሉም በእምነቱ ለፈጣሪ ተመችቶ መኖር ከቻለ ሀገሪቱ ሠላም ትሆናለች ሌላ
ምንም አያስፈልግም /ሳቅ/

ሀትሪክ፡-ፌስቡክ ትጠቀማለህ?

ምንተስኖት፡- በፊት የነበረኝን ዘግቻለሁ.. አሁን ምንም አይጠቅመኝም.. የሚሰሙትና የሚታዩት በሙሉ ደስ የማይሉና የሚረብሹ ናቸው… ዳግም መክፈትም አልፈልግም፡፡

ሀትሪክ፡-ባለፉት 10 የእግር ኳስ ተጫዋችነት ዘመንህ ፕሮፌሽናል የመሆን ፍላጎት ነበረህ?

ምንተስኖት፡- ሲጀመር ኳስ ተጨዋች እሆናለሁ ብዬ አስቤም አላውቅም ፍላጎትም አልነበረኝም ብዙ ተጨዋቾች ሲጠየቁ ለፍተን ብዙ ዋጋ ከፍለን ነው ለዚህ የበቃነው ይላሉ… እኔ ግን ኳስ ተጨዋች ለመሆን ለፍቼ
አላውቅም… መክሊቴ ነው ብዬ አስ ቤም አላውቅም፡፡ ከዚህ አንፃር እግር ኳስ ተጨዋች ከሆንኩም በኋላ ፕሮፌሽናል ለመሆን ፍላጎቱንም አልነበረኝም ለመሆንም አልሞክርኩም፡፡

ሀትሪክ፡-አገባህ… ወይስ የፍቅር ህይወት ህ ምን ይመስላል?

ምንተስኖት፡- አላገባሁም… ደግሞም ቆሜ አልቀርም /ሳቅ በሳቅ/ ለአሁኑ የፍቅር ጓደኛ የለኝም፡፡ ከኔ ጋር የተጫወቱ ከኔ ጋር የተማሩ ከእኔ ጋርም ያደጉ አብዛኛው ወይ ያገባ … አግብቶም የወለደ ..
አግብቶም የፈታ አለ… ሁለተኛም ያገባ አለ /ሳቅ/ ምን ቀረህ ለምን አታገባም የሚሉ ሰዎች ያጋጥሙኛል ገንዘብ ካለህ ትዳር መያዝ ይቻላል ብለው የሚያስቡ አሉ ይሄ ልክ አይደለም… ከባድ ነው…. ትዳር ዝም ተብሎ
አይገባበትም ትልቅ የአዕምሮ ዝግጅትና ቁርጠኝነት ይፈልጋል… ለማንኛውም ጊዜው ሲፈቅድ ትዳር የምመሰርት ይሆናል /ሳቅ/

ሀትሪክ፡- .. የመጨረሻ ቃል.. ?

ምንተስኖት፡- ለዚህች ቀን ያደረሰኝ በእድሜና በጤና የጠበቀኝ እግዚብሔር ይመስገን… እናቱ እመብርሃንን ትመሰገን፡፡ ለዚህ ያበቁኝ ቤተሰቦቼ ናቸው እነሱን አመሰግናለሁ፡፡ አሁን ገባ የተባለው የኮሮና ቫይረስ
ከእግዚአብሔር ቀጥሎ ጥንቃቄ ያስፈልገናል፡፡ ለሀገር ለሁሉም መፀለይ ይጠበቅብናል ለቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎችም ሙሉ ድጋፋቸው አይለየን ከጎናችን ሁኑ ጭንቀታችሁ ይገባናል፡፡ ደስተኛ የሚያደርጋችሁ ውጤት
አስመዝግበን እንደም ናስጨፍራችሁ ተስፋ አደርጋለሁ እናንተ ግን የሚፈለገው ውጤት እንዲገኝ እስከመጨረሻ ድረስ ድጋፋችሁ አይለየን ማለት እፈልጋለሁ አመሰግናለሁ፡፡


ክፍል አንድን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ 👇

“ሳላሀዲን ብቻ ሣይሆን እኛም እንደተመታን ነው የቆጠርነው…”ምንተስኖት አዳነ/የቅዱስ ጊየርጊስ አምበል/ ክፍል 2

 

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአማካዩ ጋር ተለያየ

መቻል እና ወልዋል ሲያሸንፉ የሀዋሳ ጨዋታዎች በአቻ ተጠናቀዋል

አቤል ያለው እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊለያዩ ነው

መድን ከአምስት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article “ሳላሀዲን ብቻ ሣይሆን እኛም እንደተመታን ነው የቆጠርነው…”ምንተስኖት አዳነ/የቅዱስ ጊየርጊስ አምበል/ ክፍል 1
Next Article ወላይታ ድቻ የእግድ ውሳኔ ተላልፎበታል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎችዜናዎችባህርዳር ከተማ

ባህርዳር ከተማ የ ተከላካዩን ወል ለማራዘም ተስማማ

fitsum Wadu By fitsum Wadu 7 months ago
“ከምወደው ቅዱስ ጊዮርጊስ የለቀቅኩት ተገፍቼ ነው” “አቶ አብነትና ደጋፊው ለኔ ባላቸው አክብሮት ደስተኛ ነኝ እኔም ለነሱ ትልቅ ክብር አለኝ.” ሄኖክ አዱኛ / ሃራስ አሌሁዳድ/
የሲዳማ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የመክፈቻ ስነስርዓት በዛሬው እለት ተካሄደ።
ኳስ ተጫዋች ባልሆን ኪቦርድ እና ድራም እጫወት ነበር። የምፈራው አጥቂ የለም ሮማን አምባዬ
​ኢትዮ- ኤሌክትሪክ ዘካሪያስ ቱጂን ከቅዱስ ጊዮርጊስ አስፈርሟል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?