መነሻ ገጽ Uncategorized ሉሲዎቹ ከታንዛኒያ ጋር ያለግብ አቻ ተለያዩ
Uncategorized

ሉሲዎቹ ከታንዛኒያ ጋር ያለግብ አቻ ተለያዩ

አጋራ
አጋራ

 

የኢትዮጵያ የሴቶች ብሄራዊ ቡድን ሉሲዎቹ ዛሬ ከታንዛኒያ አቻቸው ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 0-0 በሆነ ውጤት ሊያጠናቅቁ ችለዋል፤ በኡጋንዳ አስተናጋጅነት ለመጀመሪያ ጊዜ እየተደረገ ባለው የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ሴካፋ ሻምፒዮና ላይ የምድቡን የመጀመሪያ ጨዋታ ረቡዕ ዕለት 10 ሰአት ላይ  ከሩዋንዳ ጋር ያደረጉት ሉሲዎቹ ጨዋታቸውን 3ለ2 በሆነ ውጤት ያሸነፉ ሲሆን በእለቱም ፍልሚያቸው የድሉን ግቦች በሉዛ አበራ የ3ኛውና የ64ኛው ደቂቃ  እንደዚሁም ደግሞ በመስከረም ካንኮ የ72ኛው ደቂቃ ግቦች ነው ለማሸነፍ የቻሉት፡፡ የታንዛኒያ የሴቶች ብሔራዊ ቡድንም በፍልሚያው በመጀመሪያ ግጥሚያቸው ሩዋንዳን 3-2 በሆነ ተመሳሳይ ውጤት ያሸነፉ በመሆኑ ሁለቱ ሀገራት ኢትዮጵያ እና ታንዛኒያ እኩል 4 ነጥብ እና 1 ግብ በመያዛቸው የምድቡ መሪን ለመለየት በወጣው ዕጣ ታንዛኒያ አንደኛ መሆኗ ግጥሚያውን በኤፍ ኤም 96.3  የዕጣ ማውጣቱ ላይ ሎዛ አበራ እና ሌሎች ተጨዋቾቹ አወጣጡ ተገቢ አይደለም በሚል ተቋውሞ እንዳሰሙም እየተነገረ ይገኛል፤ የእጣ ማውጣቱ ትክክል እና ተገቢ ከሆነ ሉሲዎቹ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታ ኬንያን የሚገጥሙ ይሆናል፤፤ ታንዛኒያ ደግሞ አዘጋጇን ትገጥማለች፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
Uncategorized

ቅዱስ ጊዮርጊስ የመቶ ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገለት

ዛሬ አንጋፋውን የቅዱስ ጊዮርጊስ የስፓርት ማህበር ከገጠመው የመፍረስ አደጋ ለመታደግ የተለያዩ አካላትን...

Uncategorized

ለዋልያዎቹ መጫወትን የሚመኘው የሴሪ ኣው ክለብ ተጫዋች ማነው ?

የጣሊያን ሴሪ ኣው ክለብ ቶሪኖ ንብረት ስለሆነው አስደናቂው የአጥቂ አማካይ ተጫዋች እንንገራችሁ።...

Uncategorized

ቡናማዎቹ ተጫዋች ለማስፈረም ተስማሙ !

  በዛሬው ዕለት ግብ ጠባቂ በማስፈረም ወደ ዝውውሩ የገቡት ኢትዮጵያ ቡናማዎች ዘካሪያስ...