By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: አሊ ሱሌማን እና አህመድ ሁሴን ሀትሪክ በሰሩባቸው ጨዋታዎች ሐይቆቹ እና አዞዎቹ ጣፋጭ ድሎችን አሳክተዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ወልዋሎ ዜናዎች
ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ
ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች ድሬዳዋ ከተማ አዳማ ከተማ መቐለ 70 እንደርታ ሀዲያ ሆሳዕና የጨዋታ ዘገባ
ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ
ዜናዎች ሲዳማ ቡና የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
አርባምንጭ ከተማአዳማ ከተማመቐለ 70 እንደርታስሁል ሽረሀዋሳ ከተማኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

አሊ ሱሌማን እና አህመድ ሁሴን ሀትሪክ በሰሩባቸው ጨዋታዎች ሐይቆቹ እና አዞዎቹ ጣፋጭ ድሎችን አሳክተዋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 1 year ago
Share
SHARE

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 21ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን መርሐግብሮች በዛሬው ዕለት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታድየም ተደርገዋል።

በዕለቱ ቀዳሚ መርሐግብር ከረፋዱ 3:30 ጀምሮ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ስሁል ሽረ ተገናኝተው ሻምፒዮኑ ንግድ ባንክ 1 ለ 0 አሸንፏል።

ለ81 ደቂቃዎች ግብ ሳያስተናግድ በተጓዘው ጨዋታ ዘላለም አበበ ኪቲካ ጀማ እና ሳይመን ፒተር ለመቀነስ ሞክረው በሽረ ተከላካዮች የተመለሰውን ኳስ አግኝቶ በማስቆጠር ቡድኑን አሸናፊ ያደረገ ግብ አስቆጥሯል።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፉት ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች ከሽንፈት ርቆ በመጓዝ ላይ የሚገኝ ሲሆን በአራቱ አሸንፎ በሁለቱ ነጥብ ተጋርቷል።

- ማሰታውቂያ -

ቡድኑ ባሸነፈባቸው አራቱ ጨዋታዎች ላይም ምንም ግብ ያላስተናገደ ሲሆን ነጥቡን 28 በማድረስ ወደ 8ኛ ደረጃ ከፍ ማለት ችሏል።

የውድድር ዘመኑ አስረኛ ሽንፈት ያስተናገደው ስሁል ሽረ በበኩሉ የወራጅ ቀጠና ቆይታውን ለማራዘም ተገዷል።

በ22ኛ ሳምንት መርሐግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሊጉ መሪ ኢትዮጵያ መድን ሲገናኝ ስሁል ሽረ በበኩሉ ኢትዮ ኤሌክትሪክን ይገጥማል።

ከ9:00 ጀምሮ በተደረገው የዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ሀዋሳ ከተማ መቀሌ 70 እንደርታ ላይ አምስት ግቦችን በማስቆጠር 5 ለ 2 አሸንፏል።

የአምናው የሊጉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ አሊ ሱሌማን በ15ኛ ፤ 70ኛ እና 90+4ኛ ደቂቃዎች ላይ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ከወንድወሰን በለጠ ቀጥሎ ዘንድሮ ሀትሪክ የሰራ ሁለተኛው ተጫዋቾች ለመሆን ችሏል።

አሊ የመጀመሪያውን ግብ ከእስራኤል እሸቱ በረጅም የደረሰውን ኳስ ተቆጣጥሮ ሁለት የመቀሌ 70 እንደርታ ተጫዋቾችን በግሩም ሁኔታ በማታለል ከመረብ አዋህዷል።

በ70ኛው ደቂቃ ላይም በተመሳሳይ ከብሩክ ታደለ የደረሰውን ረጅም ኳስ ተጠቅሞ ግብ ሲያስቆጥር በ90+4 ደቂቃ ላይ ደግሞ ቸርነት አውሽ ከተከላካዮች ጀርባ የጣለለትን ኳስ ተጠቅሞ ሀትሪክ ሰርቷል።

አሊ ዛሬ ያስቆጠረችውን ግቦች ተከትሎም በውድድር ዘመኑ ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛቶች 8 አድርሷል።

በተጨማሪም በ55ኛው ደቂቃ ላይ አምበሉ ቢንያም በላይ ከእስራኤል እሸቱ የደረሰውን ኳስ እና ከሳጥን ውጪ ደጋግሞ ግቦችን እያስቆጠረ ያለው አቤኔዘር ዮሐንስ ደግሞ ዛሬም ከርቀት በአስደናቂ ሁኔታ ያስቆጠሯቸው ግቦች ሀዋሳውያን አስደሳች ቀን እንዲያሳልፉ አድርጓቸዋል።

ለመቀሌ 70 እንደርታ 10ኛው ደቂቃ ላይ የፍፁም ቅጣት ምት ያመከነው ያሬድ ብርሀኑ በ84ኛ ደቂቃ ላይ ብሩክ ኤልያስ በሙሉጌታ ወ/ጊዮርጊስ ላይ በሰራው ጥፋት የተገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ሲያስቆጥር ቦና አሊ ደግሞ ከአሸናፊ ሀፍቱ የተቀበለውን ኳስ 90+5ኛ ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።

ውጤቱንም ተከትሎ ሀዋሳ ከተማ ነጥቡን 19 በማድረስ ወደ 15ኛ ደረጃ ከፍ ሲል መቀሌ 70 እንደርታ በበኩሉ በ22 ነጥቦች 13ኛ ላይ ተቀምጧል።

በ22ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ሀዋሳ ከተማ ከ ኢትዮጵያ ቡና መቀሌ 70 እንደርታ ደግሞ ከ አርባምንጭ ከተማ ይጫወታሉ።

በዕለቱ የመጨረሻ መርሐግብር ደግሞ አርባምንጭ ከተማዎች በአህመድ ሁሴን ሶስት ግቦች አዳማ ከተማን በማሸነፍ ጣፋጭ ምሽትን አሳልፈዋል።

በጨዋታው በነቢል ኑሪ ላይ በተሰራው ጥፋት የተገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ስንታየሁ መንግስቱ በሶስተኛው ደቂቃ ላይ በማስቆጠር አዳማ ከተማን መሪ አድርጓል።

የአዳማ ከተማ መሪነት እስከ 50ኛው ደቂቃ ድረስ ቀጥሎ ነበር። በ50ኛው ደቂቃ ላይ ቡታቃ ሸመና ከአህባዋ ብሪያን የደረሰውን ኳስ በቮሊ ለአህመድ አቀብሎት አህመድ ሁሴን በማራኪ ሁኔታ መረብ ላይ አሳርፎታል።

ከዘጠኝ ደቂቃዎች በኋላ አህመድ ሁሴን በሬድዋን ሸረፉ በተሰራበት ጥፋት የተገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት በማስቆጠር ለቡድኑም ለራሱም ሁለተኛ የጨዋታውን ግብ አስመዝግቧል።

በሁለቱ ግቦች ያላበቃው አህመድ ሁሴን በ84ኛው ደቂቃ ላይ ከቻርልስ ሪባኑ በረጅም የደረሰውን በግሩም ሁኔታ ተቆጣጥሮ በአዳማ ከተማ መረብ ላይ አሳርፏል።

አህመድ የዛሬ ግቦቹን ተከትሎ በውድድር ዘመኑ ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛቶች 10 በማድረስ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን መምራት ጀምሯል።

የጨዋታውን ውጤት ተከትሎም አርባምንጭ ከተማ ነጥቡን 30 አድርሶ ወደ 4ኛ ደረጃ ከፍ ሲል አዳማ ከተማ በ19 ነጥቦች 17ኛ ላይ ተቀምጧል።

በቀጣይ ሳምንት መርሐግብር አርባምንጭ ከተማ ከመቀሌ 70 እንደርታ እንዲሁም አዳማ ከተማ ከሲዳማ ቡና ይገናኛሉ።

You Might Also Like

ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ

ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ

ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ

የሊጉ መሪ ሲዳማ በድል ሲጓዝ ኢትዮጵያ ቡና እና ኤሌክትሪክም አሸንፈዋል

መቻል እና ወልዋል ሲያሸንፉ የሀዋሳ ጨዋታዎች በአቻ ተጠናቀዋል

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ቡናማዎቹ ተከታታይ ሶስተኛ ድላቸውን ሲያስመዘግቡ ሀድያ ሆሳዕና ከሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
Next Article የአማራ ደርቢ በአቻ ውጤት ሲጠናቀቅ የጦና ንቦቹ ፈረሰኞቹን ረተዋል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎችየአፍሪካ ዋንጫ

“የደረጃውን ጨዋታ በማጫወቴ ቅር አላለኝም” ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ባምላክ ተሰማ

Habtamu Mitku By Habtamu Mitku 2 years ago
ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርሲቲ የቀድሞ አሰልጣኙን ለመቅጠር ከጫፍ ደርሷል
የጨዋታ ዘገባ | ስድስት ግቦች በተስተናገዱበት ጨዋታ ሀይቆቹና ዓፄዎቹ ነጥብ ተጋርተዋል
የጨዋታ ዘገባ | የሀድያ ሆሳዕና እና ወላይታ ድቻ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
የ2016 ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?