By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የሰሜን ደርቢ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ
Share
Notification Show More
Latest News
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችመቐለ 70 እንደርታየጨዋታ ዘገባፋሲል ከነማ

የሰሜን ደርቢ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ

ዳዊት ብርሀነ
ዳዊት ብርሀነ 1 year ago
Share
SHARE

በሁለተኛው ሳምንት ሁለተኛ ቀን የመክፈቻ ጨዋታ የተገናቹት ፋሲል ከነማ እና መቐለ 70 እንደርታ አቻ ተለያዩ። ፋሲል ከነማዎች ቅዱስ ጊዮርጊስን ካሸነፈው ቡድን ምንም ቅያሪ ሳያደርጉ ወደ ሜዳ ሲገቡ፣ የዳንኤል ፀሃዬ ቡድን በተቃራኒው 4 ቅያሬዎችን አድርገዋል። መናፍ አወል፣ ዮናስ ግርማይ፣ ተመስገን በጅሮንድ እና ኩሩቤል ሀይሉ ወጥተው አሸናፊ ሃፍቱ፣ ዘርእሰናይ ብርሃነ፣ ሸሪፍ መሐመድ እና ቤንጃሚን ኮቴ ገብተዋል።

የመጀመርያው አጋማሽ የፋሲል ከነማዎች የኳስ ቁጥጥር ብልጫ ወስደው ለመጫወት መቐለ 70 እንደርታዎች ደሞ በረጃጅም ኳሶች እድሎችን ለመፍጠር ሲሞክሩ ታይቷል። አፄዎቹ በመሀል ክፍል በኤፍሬም ሃይሉ፣ አፍቅሮት ሰለሞን እና አቤል እንዳለ አማካኝነት በአንፃራዊነት የተሻሉ ቅብብሎች በማድረግ የኳስ ቁጥጥር ብልጫን መውሰድ ችለዋል። በተለይ አፍቅሮት ሰለሞን ከመሃል ሜዳው የግራ ክፍል እየተነሳ ለማርቲን ኪዛ እና ቃልኪዳን ገዛሀኝ ያቀበላቸው ኳሶች የመጀመሪየው 45 የፋሲል ለግብ የቀረቡ እድሎች ነበሩ።

መቐለዎች የፋሲል ከነማን ተከላካይ ክፍል ወደ መሀል ሜዳ መጠጋትን ለማጥቃት ተደጋጋሚ ረጅም ኳሶችን ሲጥሉ ነበር። የዚህ እንቅስቃሴ ውጤትም በ27ኛው ደቂቃ ከተከላካይ ክፍሉ በረጅሙ የተላከውን ኳስ ያሬድ ብርሃነ ከቦና ኣሊ ጋር አንድ ሁለት ተቀባብለው አሸናፊ ሃፍቱ መትቶት የተተፋውን ኳስ ያሬድ ብርሃነ ማስቆጠር ችሏል። ከግቡ መቆጠር በኃላ ፋሲሎች ወደ ጨዋታው ለመለለስ ጫና ቢፈጥሩም አቻ ሚያደርጋቸውን ግብ ማግኘት አልቻሉም።

ሁለተኛው አጋማሽ እንደ መጀመርያው በተመሳሳይ መልኩ የፋሲል ከነማ የኳስ ቁጥጥር ብልጫ እና የምዓም አናብስቶቹ ፈጣን የመልሶ ማጥቃት እንቅስቃሴዎች የታዩበት ነበር።

- ማሰታውቂያ -

መቐለዎች ሁለተኛው አጋማሽ እንደተጀመረ በፈጣን ሽግግሮች ለግብ የቀረቡ እድሎችን መፍጠር ችለው ነበር። በተለይ ያሬድ ከበደ ለአሸናፊ የሾለከለት ኳስ ኣሸናፊ ሃፍቱ መሬት ለመሬት በቀኝ እግሩ መትቶት ከግቡ ቀኝ ለትንሽ የወጠው እንዲሁም ያሬድ ብርሃኑ ከአሸናፊ በረጅሙ የተላከለትን ኳስ ከሳጥን ውጭ በቀጥታ የመታው የዚህ እንቅስቃሴ ማሳያ ናቸው።

የኳስ ቁጥጥር ብልጫ የነበራቸው አጼዎቹ: አብዛኞቹ ቅብብላቸው በመቐለዎች ጥብቅ መከላከል እና በሜዳው የመጨረሻ ክፍል በነበራቸው ያልተሳኩ ቅብብሎች ምክንያት ግልፅ የግብ እድሎችን ለመፍጠር እንዲቸገሩ ምክንያት ሲሆኑቧቸው ታይቷል። የመቐለ 70 እንደርታ ተጨዋቾች ሳጥናቸው በቁጥር በዝተው መከላካላቸውን ያዩት ፋሲሎች በአፍቅሮት ሰለሞን እና በረከት ግዛባቸው አማካኝነት ከርቀት በሚመቱ ካሶች እድሎችን ቢፈጥሩም ኢላማቸውን የጠበቁ አልነበሩም።

የፋሲል ከነማዎች ተደጋጋሚ ማጥቃት በ65 ደቂቃ ላይ ፍሬ ማግኘት ችሏል። ከሳጥኑ አጠገብ ቢንየም ላንቃሞ በራሱ ላይ በተሰራ ጥፋት የገኘውን ቅጣት ምት ራሱ ቢንየም ላንቃሞ በሚገርም መልኩ በማስቆጠር ክለቡን አቻ ማድረግ ችሏል። በሁለት ጨዋታዎችም ሁለት የቆሙ ኳሶችን በማስቆጠር ጥሩ በአፄዎቹ ቤት ጥሩ ጅማሮውን አስቀጥሏል።

ከግቡ መቆጠር በኃላ ማጥቃታቸውን የቀጠሉት ፋሲሎች በማርቲን ኪዛ አማካኝነት ያገኙት እድል ጨዋታው ላይ በርካታ ሙከራዎችን ሲያድን የነበረው ሶፈንያስ ሰይፈ መልሶበታል። መቐለዎች በበኩላቸው በረጅም በሚጣሉ ኳሶች አልፎ አልፎ እድሎችን ፈጥረዋል። በተለይ በግብ ጠባቂው ኦቦሳጊ ስህተት ሙሉጌታ ወልደጊዮርጊስ ያገኘው ኳስ መቐለን ለአሸናፊነት ያቀረበ እድል ነበር።

በዚህም መሰረት በሁለተኛው ሳምንት የተካሄደው የሰሜን ደርቢ ጨዋታ በአቻ ሊጠናቀቅ ችሏል።

You Might Also Like

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዳዊት ብርሀነ
Follow:
Hatricksport website writer
Previous Article ኢትዮጵያ ቡና የቀድሞ ተጫዋቹን ጨምሮ ሶስት ተጫዋቾችን አስፈረመ
Next Article የጨዋታ ዘገባ | ፈረሰኞቹ የውድድር ዓመቱ ቀዳሚ ድላቸውን አስመዝግበዋል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግወልዋሎአርባምንጭ ከተማዳሰሳ

የጨዋታ ዳሰሳ | አርባምንጭከተማ ከ ውልዋሎ ዓዲግራት.ዩ

Mussie Girmay By Mussie Girmay 8 years ago
ዘወትር ማክሰኞ ለንባብ የምትበቃው ሳምንታዊዋ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ እንደተለመደው ሁሉ ነገም ለእናንተ አንባቢዎቻችን የተለያዩ የሀገር ውስጥና የባህር ማዶ ዘገባዎችን ይዛላችሁ ትቀርባለች
የጨዋታ ዘገባ | ስድስት ግቦች በተስተናገዱበት ጨዋታ ሀይቆቹና ዓፄዎቹ ነጥብ ተጋርተዋል
” ለኮስታሪካዉ የአለም ዋንጫ ለማለፍ ነዉ ጥረታችን ” ፍሬዉ ሀይለገብኤል የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ
የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ከፍተኛ አመራሮች ላይ ተጥሎ የነበረው የውጪ ጉዞ ዕገዳ ተነሳ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?