By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ፈረሰኞቹ የውድድር ዓመቱ ቀዳሚ ድላቸውን አስመዝግበዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግወልዋሎዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስ

የጨዋታ ዘገባ | ፈረሰኞቹ የውድድር ዓመቱ ቀዳሚ ድላቸውን አስመዝግበዋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 1 year ago
Share
SHARE

ቅዱስ ጊዮርጊስ የውድድር ዓመቱ ቀዳሚ ድሉን ወልዋሎ አዲግራትን 2 – 1 በመርታት አስመዝግቧል።

በጨዋታው በቅዱስ ጊዮርጊስ በኩል በፋሲል ከነማ በተረቱበት ጨዋታ ከነበረው ምርጥ 11 ዳግማዊ አርአያን እና ተገኑ ተሾመን በአማኑኤል ኤርቦ እና ፀጋ ከድር ተክተዋል። በወልዋሎ አዲግራት በኩል ደግሞ በባህርዳር ከተማ በተረታበት ጨዋታ ከነበረበው የመጀመሪያ አሰላለፍ ናሆም ሀይለማርያም እና ሰመረ ኪዳነማርያም ታዬ ጌታቸው እና ዳዋ ሆጤሳን ተክተው ገብተዋል።

በጨዋታው ቅዱስ ጊዮርጊሶች ተጭነው በመጫወት ተደጋጋሚ የግብ ዕድሎችን የፈጠሩ ሲሆን በተለይም ጨዋታው ገና በሰከንዶች ዕድሜ ሳለ ያገኙትን ዕድል ሳይጠቀሙ ቀርተዋል።

የወልዋሎ አዲግራትን የኳስ ምስረታ በማቋረጥ ያገኙትን አጋጣሚ በረከት ወልዴ አግኝቶ ለማስቆጠር ያደረገው ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል። በዚህ አጋጣሚ ግን የወልዋሎ አዲግራቶቹ ተከላካዮች ኪሩቤል ወንድሙ እና እያሱ ለገሰ ተጋጭተው እያሱ ለገሰ ከባድ ጉዳት አስተናግዷል።

- ማሰታውቂያ -

እያሱ የእግር ስብራት ጉዳት ያጋጠመው ሲሆን ወድያውኑም ለተጨማሪ ህክምና ወደ ሆስፒታል አምርቷል።

ጨዋታው ዳግም ከተጀመረ በኋላ በ7ኛው ደቂቃ ላይ ፍፁም ጥላሁን ቅዱስ ጊዮርጊስን መሪ ያደረገ ግብ ከመረብ አሳርፏል። በረጅም የተላከውን ኳስ ተገሙ ተሾመ በግሩም ሁኔታ በአየር ላይ ከተከላካዮች ጀርባ የጣለለትን ኳስ ፍፁም ጥላሁን ከመረብ አሳርፎታል። ፍፁም በቀዳሚው ጨዋታም ግብ ማስቆጠሩም የሚታወስ ነው።

ወልዋሎ አዲግራቶች በጨዋታው አቻ የሚሆኑበትን ግብ ለማግኘት የፈጀባቸው ሰባት ያህል ደቂቃዎች ብቻ ናቸው።

ቅዱስ ጊዮርጊስ በፋሲል ከነማው ጨዋታ በቀጥታ ከቅጣት ምት ከተቆጠረበት ቦታ ላይ የተገኘውን የቅጣት ምት ጋዲሳ መብራቴ አሻምቶ ኪሩቤል ወንድሙ በግንባር በመግጨት ከመረብ አሳርፏል።

በጨዋታው 19ኛው ደቂቃ ላይ የቅዱስ ጊዮርጊሱ ግብ ጠባቂ ባህሩ ነጋሽ ጉዳት አስተናግዶ በተመስገን ዮሐንስ ተቀይሮ ወጥቷል።

በቅዱስ ጊዮርጊስ በኩል በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይም በተለይም ከተገኑ ተሾመ እግር ስር በሚነሱ ኳሶች የሶስተኛው የማጥቃት የሜዳ ክፍል ላይ ጫና ለመፍጠር ጥረቶችን አድርገዋል። ቡድኑ ኳሱን ይዞ በመጫወት ረገድም ከተጋጣሚው የተሻለ አጋማሽ አሳልፏል።

ግብ ካስቆጠሩ በኋላ ያን ያህል ጠንካራ የማጥቃት እንቅስቃሴ ያላደረጉት ወልዋሎ አዲግራቶች ኪሩቤል ወንድሙን በጉዳት ምክንያት 34ኛው ደቂቃ ላይ ቀይረው ለማስወጣት ተገደዋል።

በጨዋታው የሁለተኛው አጋማሽ ላይ ቅዱስ ጊዮርጊሶች በተሻለ የማጥቃት እንቅስቃሴ ሲጀምሩ ወልዋሎ አዲግራቶች ከቆይታዎች በኋላ ዕድሎችን ለመፍጠር ጥረዋል።

በአጋማሹ ቀዳሚ ዕድል ተገኑ ተሾመ ከቀኝ መስመር አቅጣጫ የቀነሰውን ኳስ በጨዋታው ግሩም እንቅስቃሴ ያደረገው አብርሀም ጌታቸው በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቷል።

አብርሀም ጌታቸው ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላም ከሳጥን ውጪ አክርሮ የመታው ኳስ ኢላማውን ሳይጠብቅለት ቀርቷል።

በ50ኛው ደቂቃ ላይ የቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ ተጫዋች ጋዲሳ መብራቴ ከመስመር ተሻግሮ ያገኘውን ኳስ ግብ ጠባቂውን አሳልፎ ቢሞክርም ሻሂዱ ሙሰጠፋ አውጥቶታል።

ከሶስት ደቂቃዎች በኋላም ዳዊት ገብሩ ከሰለሞን ጌታቸው የደረሰውን ኳስ በአግባቡ ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

በ61ኛው ደቂቃ ላይ ተቀይሮ የገባው አማኑኤል ኤርቦ ቶሎሳ ንጉሴ ከማዕዘን ምት ያሻገረውን ኳስ በግንባር በመግጨት በ71ኛው ደቂቃ ላይ የቅዱስ ጊዮርጊስን ሁለተኛ ግብ ከመረብ አሳርፏል።

አማኑኤል ኤርቦ በቅዱስ ጊዮርጊስ ማልያ 12ኛ ቡድን ላይ ግብ ያስቆጠረ ሲሆን በአጠቃላይ በሊጉ ለፈረሰኞቹ ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛቶች 14 አድርሷል። የአርባምንጭ ፍሬ የሆነው አማኑኤል ካስቆጠራቸው 14 ግቦች መካከልም ዘጠኙ ከተጠባባቂ ወንበር ተነስቶ ያስቆጠራችው ግቦች ናቸው።

ፈረሰኞቹ ዳግም መሪ ከሆኑ በኋላ በነበሩት ደቂቃዎች ላይ ወልዋል አዲግራቶች በተደጋጋሚ ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ የግብ ክልል ደርሰዋል። ነገር ግን በቀላሉ ጠንካራ የግብ ዕድሎች ለመፍጠር ተቸግረው ጨዋታውን አጠናቀዋል።

በመጨረሻም ቅዱስ ጊዮርጊስ 2 – 1 በማሸነፍ የውድድር ዓመቱን ቀዳሚ ድል አስመዝግቧል።

በሶስተኛው ሳምንት የሊጉ መርሐግብር በመጪው መስከረም 20(ሰኞ) 10:00 ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመቀሌ 70 እንደርታ እንዲሁም ሀሙስ መስከረም 23(ሐሙስ) 1:00 ወልዋል አዲግራት ከሲዳማ ቡና ይጫወታሉ።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የሰሜን ደርቢ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ
Next Article የጨዋታ ዘገባ | አዳማ ከተማ በስንታየሁ መንግስቱ ብቸኛ ግብ አሸንፏል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎች

“ብሔራዊ ቡድናችን የጎደለውን ነገር አውቋል፤ ለአፍሪካ ዋንጫም ያልፋል” ከነዓን ማርክነህ�

መሸሻ ወልዴ By መሸሻ ወልዴ 6 years ago
ፋሲል እና ሃዋሳ ከተማ ተስተካካይ ጨዋታቸውን አሸነፉ
ፈረሰኞቹ ግብ ጠባቂ አስፈርመዋል!
ድሬዳዋ ከተማ የመስመር አጥቂዉን አስፈርሟል !!
“ሴቶችንና አገሪቷን አክብራችሁ ስለመጣችሁ አመሰግናለሁ” አሰልጣኝ ፍሬው ሃ/ገብርኤል የ20 አመት ሴቶች ብ/ቡድን አሰልጣኝ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?