By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | አዳማ ከተማ በስንታየሁ መንግስቱ ብቸኛ ግብ አሸንፏል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችባህርዳር ከተማአዳማ ከተማየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | አዳማ ከተማ በስንታየሁ መንግስቱ ብቸኛ ግብ አሸንፏል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 1 year ago
Share
SHARE

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር አዳማ ከተማ በስንታየሁ መንግስቱ ብቸኛ ግብ ባህርዳር ከተማን 1 – 0 አሸንፏል።

በባህርዳር ከተማ በኩል ወልዋሎ አዲግራትን ከረታው ቡድን የመጀመሪያ አሰላለፍ አንድ ለውጥ በማድረግ ፍፁም ፍትዓለውን በአቤል ማሙሽ ተክተው ሲገቡ በአዳማ ከተማ በኩል በስሁል ሽረ ከተረታው ቡድን ምርጥ 11 ደግሞ ቻላቸው መንበሩ ፣ ሙሴ ኪሮስ ፣ ሙሴ ከበላ እና ጋዲሳ ዋዶን በኤልያስ ለገሰ ፣ ሃይለሚካኤል አደፍርስ ፣ ዳንኤል ደምሴ እና አድናን ረሻድ ተክተው ጨዋታውን ጀምረዋል።

በሁለቱም በኩል በማጥቃት ፍላጎት ጅማሮውን ያደረገው ጨዋታው ፈጣን የጨዋታ እንቅስቃሴ የታየበት ነበር። ባህርዳር ከተማዎች በይበልጥ ኳሱን ተቆጣጥረው ወደ ፊት ለመድረስ ሲጥሩ አዳማ ከተማዎች በበኩላቸው በፈጣን ሽግግር ዕድሎችን ለመፍጠር ጥረዋል።

በጨዋታው 10ኛ ደቂቃ ላይ አዳማ ከተማዎች በነቢል ኑሪ አማካኝነት ቀዳሚ የሆኑበትን ግብ ቢያስቆጥሩም ከጨዋታ ውጪ በሚል በረዳት ዳኛው ተሽሯል። በአጋጣሚው ቢንያም አይተን ግብ ጠባቂውን ጭምር አልፎ ይዞ የገባውን ኳስ ነቢል ኑሪ ከእግሩ ስር ወስዶ አስቆጥሮ ነበር።

- ማሰታውቂያ -

ከሶስት ደቂቃዎች በኋላ ቸርነት ጉግሳ ከተከላካዮች ጀርባ የተጣለለትን ኳስ አስቆጠረው ተብሎ ሲጠበቅ የአዳማ ከተማው ግብ ጠባቂ ዳግም ተፈራ ተቆጣጥሮታል።

በ18ኛው ደቂቃ ላይ የአዳማ ከተማው የፊት አጥቂ ስንታየሁ መንግስቱ ከቢንያም አይተን በግሩም ሁኔታ የደረሰውን ኳስ በአስገራሚ መልኩ ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

ከሶስት ደቂቃዎች በኋላ በባህርዳር ከተማ በኩል ግርማ ዲሳሳ ከቸርነት ጉግሳ ተቀብሎ በግራ መስመር ይዞ የገባውን ኳስጨፍሬው ሰለሞን አግኝቶ ወደ ግብ ሞክሮ ፍቅሩ አለማየሁ ተደርቦ አውጥቶታል።

ሞቅ ባለ እንቅስቃሴ ጀምሮ የነበረው የምሽቱ ጨዋታ ከ25ኛው ደቂቃ እስከ መጀመሪያው አጋማሽ መጠናቀቂያ ድረስ ቀዝቀዝ ያለ ከሙከራም ርቆ የቆየ ሆኖ አልፏል።

የሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ልክ እንደ መጀመሪያው አጋማሽ ጅማሮ ሁሉ ጥሩ የማጥቃት ሂደት እንቅስቃሴ የተስዋለበት ነበር።

በአጋማሹ የመጀመሪያ የግብ ሙከራ በ47ኛው ደቂቃ ላይ ሲደረግ ሙሴ ኪሮስ ከአድናን ረሻድ የደረሰውን ኳስ በሳጥኑ የቀኝ አቅጣጫ ሆኖ ያደረገው ሙከራ ግብ ጠባቂው ፔፔ ሰይዶ መልሶታል።

በ53ኛው ደቂቃ ላይም ቢንያም አይተን ከስንታየሁ መንግስቱ የደረሰውን ኳስ ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

የጣና ሞገዶቹም በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይ በተለይም መነሻቸውን ከመስመር ባደረጉ ኳሶች የግብ ዕድሎች ለመፍጠር ጥረቶችን አድርገዋል። ቸርነት ጉግሳ እና ፍፁም አለሙ ያደረጓቸው ኢላማቸውን ያልጠበቁ የግብ ሙከራዎች በዚህ ሂደት ተጠቃሽ ናቸው።

ጨዋታው 67ኛ ደቂቃ ላይ ሲደርስ የመጀመሪያው ግብ ተቆጥሯል። አድናን ረሻድ ከቀኝ መስመር ወደ መሀል የቀነሰውን ኳስ ነፃ ሆኖ ያገኘው ስንታየሁ መንግስቱ ከመረብ አሳርፎታል።

ከግቡ መቆጠር ጥቂት ሰከንዶች በኋላ ባህርዳር ከተማዎች የቁጥር ብልጫ ወስደው በአዳማ ከተማ ሳጥን በተገኙበት ወቅት ቸርነት ጉግሳ ወደ ግብ ያደረገው ሙከራ በዳግም ተፈራ እጆች ላይ አርፏል።

በ73ኛው ደቂቃ ላይ ነቢል ኑሪ በግራ መስመር አቅጣጫ ይዞ የገባውን ኳስ ወደ መሀል ሲቀንሰው ያገኘው አምበሉ ቢንያም አይተን በቀጥታ ወደ ግብ ልኮት የግቡን ቋሚ ለትሞ ተመልሷል።

በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ ባህርዳር ከተማዎች ይበልጥ ጫና በመፍጠር ቢያንስ ከጨዋታው አንድ ነጥብ ለማግኘት ያደረጉት ጥረት ስኬታማ ሳይሆን ቀርቷል።

በመጨረሻም አዳማ ከተማ የውድድር ዓመቱን ቀዳሚ ድል በባህርዳር ከተማ ላይ ተቀዳጅቷል።

በሶስተኛው ሳምንት ጨዋታዎች ማክሰኞ መስከረም 10(ማክሰኞ) ረፋድ 3:30 ጀምሮ አዳማ ከተማ ከወልቂጤ ከተማ እንዲሁም በዕለቱ ምሽት 1:00 ጀምሮ ባህርዳር ከተማ ከሀድያ ሆሳዕና ይጫወታሉ።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | ፈረሰኞቹ የውድድር ዓመቱ ቀዳሚ ድላቸውን አስመዝግበዋል
Next Article ጋቶች ፓኖም ወደ ኢትዮጵያ መድኅን አመራ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ወላይታ ድቻፋሲል ከተማየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

የጨዋታ ዘገባ | አፄዎቹ ተከታታይ ድል አስመዘገቡ

kidus Yoftahe By kidus Yoftahe 5 years ago
ታድሷል ተብሎ ያልታደሰ መሳዩ አንጋፋው ስታዲየም…!
የአዲስ አበባ ዋንጫ የኮከቦቹ ዋንጫ ኢትዮጵያ ደርሷል
“ኢትዮጵያ ታሳዝነኛለች”    “ሀገሬን የማገልገል ስሜቴን አሰልጣኞች ገድለውታል”      ዳዊት እስጢፋኖስ
የኢትዮጵያ ቡና የቀድሞ እግር ኳስ ተጨዋቾች ማህበር ከብራዚል ባስመጣው የእግር ኳስ ባለሙያ ስልጠና ተሰጠ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?