By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ነገሌ አርሲ ድል ሲቀናው ደርቢው ያለ ግብ ተጠናቋል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ባህርዳር ከተማየጨዋታ ዘገባፋሲል ከነማነጌሌ አርሲየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግወልዋሎዜናዎች

ነገሌ አርሲ ድል ሲቀናው ደርቢው ያለ ግብ ተጠናቋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 2 months ago
Share
SHARE

የ11ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ መደረግ ጀምረዋል

የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ11ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ መደረግ ሲጀምሩ አዲስ አበባ ስታድየም ላይ በተደረጉት ጨዋታዎች ነገሌ አርሲ ድል ሲቀናው ተጠባቂ የነበረው የደርቢ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል።

በሳምንቱ መክፈቻ በሆነው ጨዋታ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲን የገጠመው ነገሌ አርሲ በአሸብር ውሮ የፍፁም ቅጣት ምት ግብ 1 ለ 0 አሸንፏል።

ከቤ ብዙነህ በኪሩቤል ወንደሙ በተሰራበት ጥፋት የተገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት አሸብር ውሮ አስቆጥሮ ነገሌ አርሲን አሸናፊ አድርጓል።

- ማሰታውቂያ -

ነገሌ አርሲ ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን 16 ሲያደርስ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ በበኩሉ በነበረው 8 ነጥቦች ለመቆየት ተገዷል።

በ12ኛው ሳምንት ነገሌ አርሲ ከድሬዳዋ ከተማ እንዲሁም ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ደግሞ ከባህርዳር ከተማ ይጫወታሉ።

ከ10:00 ጀምሮ በአንፃራዊነት በበርካታ ደጋፊዎች ታጅቦ የተደረገው የባህርዳር ከተማ እና የፋሲል ከነማ ጨዋታ ግብ ሳይቆጠርበት 0 ለ 0 ተጠናቋል።

የጨዋታው የመጀመሪያ 20 ደቂቃዎች የተቀዛቀዘ የሜደ ላይ እንቅስቃሴ የታየባቸው ሲሆን በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይ በሁለቱም ቡድኖች በኩል መሪ መሆን የሚችሉባቸውን የግብ ዕድሎች ፈጥረዋል።

በተለይም የተሻሉ ዕድሎችን መፍጠር ችለው የነበሩት የጣና ሞገዶቹ የፋሲል ከተማን የኋላ ክፍል በሚገባ መፈተን ችለው ነበር።

አማኑኤል ገብረሚካኤል በ21ኛው ደቂቃ ላይ ከወንድወሰን በለጠ ከቀኝ የሳጥኑ አቅጣጫ የተቀነሰለትን ኳስ ሳይደርስበት ቀርቷል።

በ22ኛው ደቂቃ ላይም አማኑኤል ከመሳይ አገኘሁ በረጅም የተሻገረለትን ኳስ በአግባቡ ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

በአፄዎቹ በኩል በተለይም በግራ መስመር ባደላው የማጥቃት እንቅስቃሴያቸው የተጋጣሚያቸውን የኋላ መስመር ለመፈተን ጥረቶችን አድርገዋል።

በ21ኛው ደቂቃ ላይ አቤኔዘር ዮሐንስ ከሳጥን ውጪ ያደረገው እና ዋሳዋ ጄኦፍሪ በ39ኛው ደቂቃ ላይ ከቅጣት ምት ያደረጓቸው ሙከራዎች ፔፔ ሰይዶን የፈተኑ አጋጣሚዎች ነበሩ።

በሁለተኛው አጋማሽ ባህርዳር ከተማዎች በይበልጥ ተሽለው ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል መድረስ ችለዋል።

በፋሲል ከነማ በኩልም በፈጣን ሽግግሮች ዕድሎችን ለመፍጠር ጥረቶችን አድርገዋል።

ነገር ግን በሁለቱም በኩል በተጋጣሚ የሳጥን ክልል ሲደርሱ በተጠበቀው ልክ ጠንካራ የግብ ሙከራዎች አላደረጉም።

መሳይ አገኘሁ በባህርዳር ከተማ በኩል ዳግም አወቀ ደግሞ በፋሲል ከነማ በኩል ከሳጥን ውጪ ያደረጓቸው ጠንካራ የግብ ሙከራዎች በግብ ጠባቂዎቹ ተመልሰዋል።

ውጤቱን ተከትሎ ፋሲል ከነማ ነጥቡን 21 ያደረሰ ሲሆን ባህርዳር ከተማ በበኩሉ 14 ነጥቦች ላይ መድረስ ችሏል።

በ12ኛው ሳምንት የሊጉ መርሐግብር ፋሲል ከነማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን ባህርዳር ከተማ ደግሞ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲን የሚገጥሙ ይሆናል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የተከላካይ አማካዩ ወደ ኢትዮጵያ መድን አምርቷል
Next Article መቐለ እና ሀድያ ሆሳዕና ወሳኝ ድል አሳክተዋል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎችኢትዮጵያ ንግድ ባንክኢትዮጵያ መድህን

አሰልጣኝ በጸሎት ልዑልሰገድ ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ….

ዮሴፍ ከፈለኝ By ዮሴፍ ከፈለኝ 3 years ago
የፕሪሚየር ሊጉን ቀጣይ ጨዋታዎች የሚያስተናግዱ ከተሞች ይፋ ተደርገዋል
ታሪካዊው ክለብ በውስብስብ ፈተናዎች ውስጥ እስከ መቼ ?
“ሀይሌንና ቀነኒሳን በቪዲዮ እያየሁ ማደጌ ለዛሬው የአትሌቲክስ ህይወቴ ጠቅሞኛል፤አለም ሻምፒዮናና ኦሎምፒክ ላይ ታሪክ ማፃፍ ህልሜ ነው” የኦቷዋ የ10ኪ.ሜ አሸናፊ አትሌት አንድአምላክ በልሁ
አፄዎቹ በቡናማዎቹ የመጀመሪያ ሽንፈት ሲቀምሱ ባህርዳር እና መድንም አሸንፈዋል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?