በ23/2/2017ዓ/ም ሀምበርቾ እግር ኳስ ቡድን ከ ወልቂጤ ከተማ እግር ኳስ ቡድን ጋር በነበረዉ _ጨዋታ የሀምበርቾ ኳስ እግር ቡድን በሜዳ ላይ ያለመገኝታቸውን የጨዋታና የውድድር አመራሮች ሪፓርት ቀርቧል፡፡ በዚህም መሠረት፥
ሀ. የጨዋታ ፕሮግራም ወጥቶለት በሰዓቱ ቀርቦ ውድድሩን ያላከናወነው ሀምበርቾ እግር ኳስ ቡድን በ2017 ዓ/ም ለውድድሩ ማስፈጸሚያ በወጣው ደንብ አንቀጽ 5 ተራ ቁጥር 3 እና 5 መሰረት ብር 60,000 (ስልሳሽህ ብር) ቅጣት 26/02/17 ዓ/ም እስከ 03/03/17 ዓ/ም ድረስ ባሉት 7 ቀናት ዉስጥ በቅጣት ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ገቢ እንዲያደርጉ በተሰጠዉ 7ቀን የጊዜ ገደብ ውስጥ ገንዘቡን ገቢ የማያደርጉ ከሆነ በየቀኑ 2% ሁለት በመቶ ቅጣት ተጨምሮ እንዲከፍሉ ተወስኗል፡፡
ለ. ሀምበርቾ እግር ኳስ ቡድን 17/02/2017 እና 23/02/2017 ዓ/ም እንጅባራ እግር ኳስ ቡድን እና ወልቂጤ ከተማ እግር ኳስ ቡድን ጋር በነበረዉ ጨዋታ የሀምበርቾ እግር ኳስ ቡድን 2 (ሁለት) ጊዜ በተከታታይ ወይም በዚያው የውድድር ዓመት በተለያየ ጊዜ በጨዋታ ሜዳ ባለመገኝቱ ፎርፌ በመስጠታቸው በተሻሻለው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዲሲፕሊን መመሪያ ምዕራፍ 3 አንቀጽ 69 ተራ ቁጥር 14 መሰረት ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ውድድር መሰረዛቸዉን ኮሚቴው ወስኗል፡፡



