መነሻ ገጽ Covid-19 የኢትዮጵያ ቡና ተጨዋቾች ዛሬ የኮቪድ ምርመራ ይደረግላቸዋል
Covid-19ኢትዮጵያ ቡናዜናዎች

የኢትዮጵያ ቡና ተጨዋቾች ዛሬ የኮቪድ ምርመራ ይደረግላቸዋል

አጋራ
አጋራ



ክለቡ ከቀናቶች በኋላ ዝግጅቱን ይጀምራል


የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የዘንድሮ የውድድር ዘመን ጅማሬን በናፍቆትና በጉጉት እየጠበቀ የሚገኘው ኢትዮጵያ ቡና ዛሬ ከእዚህ ሰዓት ጀምሮ በህክምና ባለሙያዎች ለቡድኑ ተጨዋቾች የኮቪድ ምርመራ የሚያደርግላቸው መሆኑ ታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የእዚህ ዓመት የውድድር ተሳትፎ ላይ ጠንካራ ቡድንን ይዞ ይቀርባል ተብሎ የሚጠበቀው ኢትዮጵያ ቡና ለአዲሱ የውድድር ዘመን በስኳዱ ላሰባሰባቸው በርካታ ተጨዋቾች ዛሬ የኮቪድ ምርመራን እንዲያደርጉ ጥሪ ባደረገበት ሁኔታ አብዛኛዎቹ ተጨዋቾች ለምርመራው በስፍራው ለመድረስ የተቃረቡ ሲሆን ክለቡን በዝውውር መስኮት ከመከላከያ የተቀላቀለው አበበ ጥላሁን ወደ አዲስ አበባ ከሰዓት የሚደርስ በመሆኑ ለእሱ ለብቻው ይኸው ምርመራ የሚደረግለት መሆኑም ታውቋል፡፡

ኢትዮጵያ ቡና ለዘንድሮው የሊግ ውድድር ተሳትፎ ከማምራቱ በፊት እስካሁን የቡድኑ ተጨዋቾች የሚያርፉበትን ካምፕ እና የመለማመጃ ስፍራውን ከኮቪድ ወረርሽኝ ነፃ ለማድረግ አስፈላጊውን የፅዳት ፕሮግራም ያደረገ ሲሆን ከዛም ባሻገር ቡድኑ ባወጣው ጨረታም አሁን ላይ ስሙን ማወቅ ባንችልም የክለቡ አስመጋቢ የምግብ ባለሙያም መታወቁ ተገልጿል፡፡

ኢትዮጵያ ቡና በዛሬው ዕለት ለተጨዋቾቹ ይሄን የኮቪድ ምርመራ ካደረገ በኋላም የፕሪ-ሲዝን ዝግጅቱን ቅዳሜ ወይንም ደግሞ ሰኞ ሊጀምሩ እንደሚችሉም እየተገለፀ ይገኛል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...