መነሻ ገጽ አፍሪካ የኢትዮጵያ ተጋጣሚ ኒጀር ሁለተኛ የወዳጅነት ጨዋታዋን አሸነፈች
አፍሪካዜናዎች

የኢትዮጵያ ተጋጣሚ ኒጀር ሁለተኛ የወዳጅነት ጨዋታዋን አሸነፈች

አጋራ
አጋራ

ለአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ የሶስተኛና አራተኛ ጨዋታዎች ኢትዮጵያን በደርሶ መልስ የሚገጥመው የኒጀር ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ምሽት ባደረገው ሁለተኛ የወዳጅነት ጨዋታ የሴራሊዮን አቻውን አንድ ለምንም ረታ፡፡

አዲሱ የኒጀር ብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፈረንሳያዊው ዣን-ሚሸል ካቫሊ ከቡድኑ ጋር ሁለተኛ ድላቸውን በማስመዝገብ ካሁኑ የደጋፊውን ቀልብ መሳብ ችለዋል። አሰልጣንኙ ቡድኑን ባለፈው ሳምንት ከተረከቡ በኋላ ያደረጓቸውን ሁለት ጨዋታዎች በማሸነፍ የ100% የአሸናፊነት ግስጋሴያቸውን አስቀጥለዋል። አሰልጣኙ ሁለት ጨዋታዎችን አድርገው ሁለቱንም ሲያሸንፉ ምንም ግብ ሳይቆጠርባቸው ሶስት ግቦችን አስመዝግበዋል።

በጄኔራል ሴኚ ኩንቼ ብሔራዊ ስታዲየም የተደረገውን ጨዋታ ኒጀር አንድ ለባዶ ስታሸንፍ ግቡን ያስቆጠረው ለቡርኪናፋሶው ራሂሞ ክለብ የሚጫወተው ኢሳ ጂብሪላ ነው፡፡

ኢሳ ጅብሪላ ባለፈው ቅዳሜ ቡድኑ ቻድን ሁለት ለምንም ሲረታ ሁለተኛውን ግብ ከመረብ ማሳረፉ ይታወሳል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...