By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: እንየው ካሳሁን ከፋሲል ከነማ የወጣበት መንገድ አነጋጋሪ ሆኗል
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችድሬዳዋ ከተማፋሲል ከነማ

እንየው ካሳሁን ከፋሲል ከነማ የወጣበት መንገድ አነጋጋሪ ሆኗል

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 5 years ago
Share
SHARE

 

“ለጎንደር ህዝብና ለፋሲል ደጋፊ ያለኝ ፍቅር የተለየ ነው፤ፈልጌ ሳይሆን ተገፍቼ ነው የወጣሁት”
እንየው ካሳሁን /ድሬዳዋ ከተማ/

ለድሬዳዋ ከተማ የፈረመው እንየው ካሳሁን ከምወደው ክለብ የወጣሁት ተገድጄ ነው ሲል ተናገረ።

ተጨዋቹ በተለይ ለሃትሪክ እንደተናገረው ከምወደው ክለብ እወጣለሁ ብዬ አስቤም አላውቅም ነበር ብሏል። “የቀረበልኝ ደመወዝ ከጠየኩት ጋር ባይገናኝም ክለቡን ስለምወደው ተስማምቻለሁ በቅድሚያ ክፍያ መጠን ላይም አልተከራከርኩም ነገር ግን የቅድሚያ ክፍያውን የምንሰጥህ ጥቅምት ወር ላይ ነው አሉኝ እሺ ለጥቅምቱም ቼክ ጻፉልኝ ስላቸው አንጽፍልህም እመነን ሲሉኝ ተበሳጨሁ ለሌላው የፊርማ ክፍያ እየሰጡ እኔን ለምን ይከለክሉኛል? ለዚህ ነው እንደማልፈለግ የገባኝ”ሲል ተናግሯል።

- ማሰታውቂያ -

አሰልጣኝ ስዩም ከበደ በበኩሉ “እንደምንፈልገውማ ያውቃል የቦርድ አባላቱና ኮሚቴው ከአንዴም ሁለቴ ያናገሩት ለዚያ ነው እኔና የቡድን መሪው አቶ ሀብታሙ ዘዋለ ፌዱሬሽን ሆነን ለፊርማ ሁለት ቀን ስንጠብቀው መጣሁ እያለ ቀርቷል አልተገኘም ይሄ መቀጠል ስላልፈለገ ይመስለኛል በቦታው ተመራጭ የነበረው ሰዒድ ሀሰን ነበር በመጎዳቱ እንየው እንዲተካው ተደርጎ ጥሩ አቋሙን አሳይቷል በፋሲል ከነማ የገጠመው ስኬትን ማሰብም ነበረበት” በማለት ከፋሲል የለቀቀው መቀጠል ባለመፈለጉ ነው የሚያስብል አስተያየቱን ሰጥቷል።

እንየው ካሳሁን ግን የአሰልጣኙን ሃሳብ ያስተባብላል “ትክክል አይደለም ከክለቡ አመራሮች ጋር በውል ማደስ ዙሪያ ሳንስማማ ፌዴሬሽን እየጠበቅንህ ነው ናና ፈርም ማለታቸው ተገቢም አልነበረም ክርክር ላይ ባለ ጉዳይ ገና ሳንስማማ የእነሱ እኔን ፌዴሬሽን መጠበቅ ትክክል አልነበረም ያለው እውነት ይሄ ነው” ብሏል። “ድሬዳዋ ከተማዎች ሙሉ ክብር ሰጥተው እንዴት እንደሚፈልጉኝ አሳይተው አስፈርመውኛል እነሱንም አመሰግናለሁ ለድሬዳዋ ከተማ የምችለውን ለማድረግ ተዘጋጅቻለሁ” ያለው እንየው ካሳሁን አጽንኦት የሰጠው ለጎንደር ህዝብና ለፋሲል ደጋፊዎች ስላለው ፍቅር ነው። “ለጎንደር ህዝብና ለፋሲል ከነማ ደጋፊ ትልቅ ክብርና ፍቅር አለኝ መቼም ከልቤ አይወጡም ለዚህ የደረስኩት እነሱ ከጎኔ በመሆናቸው ነው ለሁሌውም መልካሙን ሁሉ እመኝላቸዋለሁ ስለ እውነት ለመናገር ለጎንደር ህዝብና ለፋሲል ደጋፊ ያለኝ ፍቅር የተለየ ነው፧ ፈልጌ ሳይሆን ተገፍቼ ነው የወጣሁት ይህን እንደሚረዱኝ ተስፋ አደርጋለሁ” ብሏል።

በዚህ ቅሬታ ዙሪያ ከሃትሪክ ጥያቄ የቀረበላቸው የክለቡ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አቢዮት ብርሃኑ በሰጡት ምላሽ.. “እንየው ካሳሁን ውሉን እንዲያድስ ለማድረግ ሞክረን አልተሳካልንም ነገር ግን ክለቡ ከተጨዋች በላይ ነውና ጉዞው ይቀጥላል” ሲሉ ተናግረዋል። አቶ አቢዮት እንዳሉት ” ከበጀት መዘግየትና መፍጠን ጋር ተያይዞ አንዳንዴ እንዲህ አይነት ነገር ሊከሰት ይችላል እስካሁንም በጀት አልተለቀቀልንም ነባር ተጨዋቾቻችን ውል ሲያድሱ ቼክ ጠይቀውን አያውቁም እሱ መጠየቅ ግን መብቱ ነው ያም ሆኖ መስማማት ባለመቻሉ ክለቡን ተሰናብቷል ለሌላው ቼክ እየሰጡ ለኔ ለምን ከለከሉ ላለው ማንኛውም ተጨዋች ራሱን ወክሎ እንጂ ሌሎችን እያየ እንቢ ወይም እሺ ማለት ተገቢ አይመስለኝም እንደ ተጨዋች ሊተካ የሚችልና በቀላሉ የማይተካ ተጨዋች ሲኖር የምናቀርበው መደራደሪያና የምናስተላልፈው ውሳኔ ሊለያይ ይችላል” ሲሉ መልሰዋል።

“በክለባችን የማይጣስ መርህ አለ በኛ በኩል የማናደርገውን ቃል አንገባም የተናገርነውን ደግሞ እንፈጽማለን ባለፉት 5 አመታት ጠንካራ ሆነን የሊጉንም የጥሎ ማለፍ ዋንጫ ያነሳው በሻምፒየንስ ሊግም ይሁን በኮንፌዴሬሽን ካፕ የምንካፈለው በዚህ ጥንካሬያችን ነው” በማለት ስራ አስኪያጁ አቶ አቢዮት ብርሃኑ ለሃትሪክ ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article ሀብታሙ ታደሰ(ቁልጭ) ሀድያ ሆሳዕናን ተቀላቅሏል!!
Next Article ኢትዮጵያ ቡና የአማካይ ስፍራ ተጫዋች አስፈርሟል!!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግሀዋሳ ከተማቅድመ ዳሰሳወልቂጤ ከተማ

ቅድመ ዳሰሳ | ሀዋሳ ከተማ ከወልቂጤ ከተማ

Seble Berhanu By Seble Berhanu 6 years ago
የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አሳክቷል !!
ከምሽቱ የዋልያዎቹ እና የኬፕ ቨርዴ ጨዋታ በኋላ የአሰልጣኞች አስተያየት
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በአሜሪካ የዋሊያዎቹ ጉዞ ዙሪያ ማብራሪያ ሰጠ
ኢትዮጵያ ቡና የተጫዋቹን ውል አድሷል።
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
Welcome Back!

Sign in to your account

Lost your password?